አጠቃላይ ገጽታ
የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ከዞኑ ርዕሰ መዲና ሶዶ ከተማን አዋስኖ የሚገኝና የቆዳ ስፋቱም 347.8 ካሬ ኪሎ ሜትር ሲሆን በ31 የገጠር ቀበሌዎች እና በ6 የማዘጋጃ ቤት ከተሞች የተዋቀረ ነው፡፡ በአስተዳደሩ የሚገኙ የኢንቨስትመንት አማራጮች፤ የማዕድን ሀብት ክምችትና የቱሪስት መስህቦች እንደሚከተለዉ ቀርበዋል፡፡
1.1 ከባህር ወለል ከፍታ
ከባህር ወለል በላይ ከ1,501 እስከ 2,958 ሜትር ከፍታ ያላቸው የመሬት ገጾች አሉት፡፡
1.2 የአየር ንብረት
የወረዳው አግሮኢኮሎጂን በተመለከተ 13% ደጋ እና 87% ወይና ደጋ ነዉ፡፡ የዓመቱ አማካይ የሙቀት መጠን 12.6--27.5 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ነው፡፡ አማካይ ዓመታዊ የዝናብ መጠን ከ1,201 እስከ 1,600 ሚሊ ሜትር ነው፡፡
1.3 ሥነ-ሕዝብ
በ2009 ዓ.ም ከዞኑ ፋ/ኢ/ል/መምሪያ በተገኘው የስታትስቲክስ መረጃ መሠረት የወረዳው አጠቃላይ የሕዝብ ብዛት 179,109 ሲሆን የሕዝብ ጥግግት 600 በስኳየር ኪ/ሜትር ነው፡፡
. የመሠረተ ልማት አቅርቦት ሁኔታ
2.1 መንገድ
ወረዳው ውስጥ 36.5 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ፣ 18 ኪ/ሜትር የጠጠር እና 642.3 ኪ/ሜትር ጥሪጊያ መንገዶች ሲኖረው በአብዘኛው የወረዳው ቀበሌዎች ከዞንና ከክልል ብሎም ወረዳን ከወረዳ እንዲሁም እያንዳንዱን የገጠር ቀበሌም ጭምር በዋናና በውስጥ ለውስጥ መንገዶች እርስ በእርስ የተገናኘ ነው፡፡
2.2 ስልክ፣ ኢንተርኔት እና የፖስታ አገልግሎት
የሞባይልና የመደበኛ ስልክ አገልግሎት፣ እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎት የሚሰጡ የግል ንግድ ማዕከላት እየተከፈቱ ይገኛሉ፡፡ አንድ የፖስታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በሶዶ ከተማ ይገኛል፡፡
2.3 መብራት
በወረዳው ውስጥ የሚገኙ የከተማ አከባቢዎች 24 ሰዓት የሃይደሮ ኤሌክትሪክ ኃይል መብራት አገልግሎት ያገኛሉ፡፡
2.4 የመጠጥ ውኃ አቅርቦት
የመጠጥ ውኃ አቅርቦትን በተመለከተ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ የእጅ ጉድጓድ ( ) 28፣ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ ጥልቅ ጉድጓድ ( ) 35፣ ጥልቅ ጉድጓድ ስርጭት ( ) 5፣ የምንጭ ውኃ ስርጭት ( ) 12፣ ምንጭ በቦታው ማጎልበት ( ) 54 ይገኛሉ፡፡ የወረዳው የመጠጥ ውኃ ሽፋን 65.84% ሲሆን በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ችግር ለማቃለል የጥልቅ ጓድጓድ ውኃ አገልግሎት ለመስጠት በተለያዩ ቀበሌዎች መስመር እየተዘረጋ ይገኛል፡፡
2.5 የገንዘብ ተቋማት፡-
የወረዳው ነዋሪዎች ዘመናዊ የባንክና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎትን ከወረዳው ዋና ከተማ ሶዶ ውስጥ ከሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት ያገኛሉ፡፡
. የማህበራዊ አገልግሎት
3.1 ጤና
3.2 ትምህርት
መዋዕለ ሕጻናት ት/ቤት -------------------------- 6
አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-4ኛ ክፍል) -------------- 2
አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-8ኛ ክፍል) -------------- 34
ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (9-10ኛ ክፍል) ------------ 4
መሰናዶ (11-12ኛ ክፍል) --------------------------- 1
. በመስኖ የሚለማ የእርሻ መሬት ሁኔታ
በወረዳው ውስጥ 5 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ በመሆናቸው የአከባቢው አርሶ አደር ተጠቃሚ ሲሆን ለአብነት ኮተገንት መስኖ በሼላ ቦርኮሼ ቀበሌ (60 ሄ/ር)፣ ጫሬ ሀማሳ መስኖ በቦሳ ቃጫ ቀበሌ (25.18 ሄ/ር)፣ ታካቻ መስኖ በሼላ ኮዶ ቀበሌ (150 ሄ/ር)፣ ታንዶ መስኖ በዛላ ሻሻ ቀበሌ (35 ሄ/ር)፣ እና ቡሻ መስኖ በቡሻ ቀበሌ (25 ሄ/ር) የመስኖ ፕሮጀክቶች 100% አገልግሎት መስጠት ባይጀምሩም ለአከባቢው ማህበረሰብ ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ አንጻር አዎንታዊ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ ወረዳው ካለው የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውኃ አቅርቦት ለአብነት ወንዞች (ሀማሳ ወንዝ፣ ሊንታላ፣ ዋጃ፣ ቢሳሬ፣ ታካቻ እና ልቂምሴ ወንዝ) ከመኖሩ አንጻር እስካሁን በመስኖ የለማው መሬት መጠን በጣም ዝቅተኛ ከመሆኑም ባሻገር ወረዳው ከፍተኛ ለመስኖ አገልግሎት ሊውል የሚችል የውኃ ፖቴንሻል እንዳለ፣ ከፍተኛ የዝናብ መጠን መኖሩ እና ለም ዐፈር መኖሩ ለእርሻ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡
. በወረዳው የሚመረቱ ዋና ዋና ምርቶች
5.1 ዓመታዊ ሰብሎች
በቆሎ፣ ጤፍ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ሽንብራ፣ ገብስ፣ የሥራ ሥር ሰብሎች፣ አትክልት (ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማትም)፣ ቅመማ ቅመም ምርት፣
5.2 ቋሚ ሰብሎች
ፍራፍሬ (ሙዝ፣ ማንጎ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን)፣ እንሰት፣ ቡና፣
. ለኢንቨስትመንት የተዘጋጀ መሬት
ተ.ቁ
የቀበሌው ስም
ለኢንዱስትሪ በሄ/ር
ለንግድና አገልግሎት በሄ/ር
ለማህበራዊ አገልግሎት በሄ/ር
ለገጠር እርሻ ልማት በሄ/ር
1
ዳልቦ ከተማ
3.51 ሄ/ር
774.54
13.25 ሄ/ር
------
2
ሀባ ገረራ
---
-----
130 ሄ/ር
ምንጭ፡- ዳልቦ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት
ማሳሰቢያ፡- ለገጠር እርሻ ኢንቨስትመንት የተለዩ ቦታዎችን በተመለከተ በሀባ ገሬራ ቀበሌ ቀበሌ 130 ሄ/ር መሬት በተጨማሪ በወረዳዉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት አማካይነት በተፋሰስ ሊለሙ የሚችሉ በተለያዩ ቀበሌዎች የወል መሬት ሰርቨይ ተደርጎ የተካለለው ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሊውል የሚችል ሲሆን ከዳልቦ ማዘጋጃ ቤት በተገኘው መረጃ መሠረት ከ791 ሄ/ር በላይ መሬት ለተለያዩ አገልግሎቶች በከተማው መሠረታዊ ፕላን መሠረት የተዘጋጀ መሆኑን ታሳቢ ሊደረግ ይገባል፡፡
. ለኢንቨስትመንት ያለው አመቺነት
7.1 ለግብርና
7.2 ለአግሮ ኢንዱስትሪ
7.3 ለማህበራዊ አገልግሎት
የወረዳው የጤና ሽፋን 104.6% የደረሰ ቢሆንም በላቦራቶሪ እና በግል ፋርማሲ ተቋማት ሽፋን ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤
የመዋዕለ ሕጻናት እና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ብዛት ዝቅተኛ መሆኑ እንዲሁም በከፍተኛ የት/ት ተቋማት ወይም ኮሌጆች በወረዳው ውስጥ ያለመኖር ለግል ባለሀብት በመስኩ መሰማራት አመችነቱን ይጠቁማል፡፡
7.4 ለሆቴል፣ ለሪዞርት፣ ለሎጅ፣ ለመዝነኛ ፓርክ እና ቱሪዝም አገልግሎት
7.5 ለማዕድን፣ ኢነርጅ እና ለኮንስትራክሽን ዘርፍ
. የኢንቨስትመንት አማራጭ ዕድሎች
8.1 ግብርና ዘርፍ
8.2 በማህበራዊና በአገልግሎት ዘርፍ
8.3 በኢንዱስትሪ ዘርፍ
የኢንዱስትሪ ፖቴንሻል ሰርቨይ / / ጥናት መሠረት በከተማው ውስጥ
Copyrights 2019. . All Rights Reserved.
Developed by SNNPRS-SITB & SNNPRS-wza