. አጠቃላይ ገጽታ
የቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ከዞኑ ርዕሰ መዲና ሶዶ በስተሰሜን ምዕራብ በ29 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝና የቆዳ ስፋቱም 271.1 ካሬ ኪሜትር ሲሆን በ27 የገጠር ቀበሌዎች እና በ5 የማዘጋጃ ቤት ከተሞች የተዋቀረ ነው፡፡ በአስተዳደሩ የሚገኙ የኢንቨስትመንት አማራጮች፤ የማዕድን ሀብት ክምችትና የቱሪስት መስህቦች እንደሚከተለዉ ቀርበዋል፡፡
1.1 ከባህር ወለል ከፍታ
ከባህር ወለል በላይ ከ501 እስከ 2,500 ሜትር ከፍታ ያላቸው የመሬት ገጾች አሉት፡፡
1.2 የአየር ንብረት
የወረዳው አግሮኢኮሎጂን በተመለከተ 5% ደጋ እና 95% ወይና ደጋ ነዉ፡፡ የዓመቱ አማካይ የሙቀት መጠን 17.6--22.5 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ነው፡፡ አማካይ ዓመታዊ የዝናብ መጠን ከ1,201 እስከ 1,600 ሚሊ ሜትር ነው፡፡
1.3 ሥነ-ሕዝብ
በ2009 ዓ.ም ከዞኑ ፋ/ኢ/ል/መምሪያ በተገኘው የስታትስቲክስ መረጃ መሠረት የወረዳው አጠቃላይ የሕዝብ ብዛት 219,142 ሲሆን የሕዝብ ጥግግት 788 በካሬ ኪ/ሜትር ነው፡፡
II. የመሠረተ ልማት አቅርቦት ሁኔታ
2.1 መንገድ
ወረዳው ውስጥ 36.5 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ፣ 35.5 ኪ/ሜትር የጠጠር እና 1575 ኪ/ሜትር ጥሪጊያ መንገዶች ሲኖሩት በአብዘኛው የወረዳው ቀበሌዎች ከዞንና ከክልል ብሎም ወረዳን ከወረዳ እንዲሁም እያንዳንዱን የገጠር ቀበሌም ጭምር በዋናና በውስጥ ለውስጥ መንገዶች እርስ በእርስ የተገናኘ ነው፡፡
2.2 ስልክ፣ ኢንተርኔት እና የፖስታ አገልግሎት
የሞባይልና የመደበኛ ስልክ አገልግሎት፣ እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎት የሚሰጡ የግል ንግድ ማዕከላት እየተከፈቱ ይገኛሉ፡፡ አንድ የፖስታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በወረዳው ዋና ከተማ በሆነችው አረካ ከተማ ውስጥ ይገኛል፡፡
2.3 መብራት
በወረዳው ውስጥ የሚገኙ የከተማ አከባቢዎች 24 ሰዓት የሃይደሮ ኤሌክትሪክ ኃይል መብራት አገልግሎት ያገኛሉ፡፡
2.4 የመጠጥ ውኃ አቅርቦት
የመጠጥ ውኃ አቅርቦትን በተመለከተ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ የእጅ ጉድጓድ (hand dug wells fitted with hand pump) 68፣ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ ጥልቅ ጉድጓድ (shallow wells fitted with hand pump) 70፣ ጥልቅ ጉድጓድ ስርጭት (deep wells distribution) 8፣ የምንጭ ውኃ ስርጭት (springs with distribution) 7፣ ምንጭ በቦታው ማጎልበት (Spot spring) 63 ይገኛሉ፡፡ የወረዳው የመጠጥ ውኃ ሽፋን 62.34% ሲሆን በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ችግር ለማቃለል የጥልቅ ጓድጓድ ውኃ አገልግሎት ለመስጠት በተለያዩ ቀበሌዎች መስመር እየተዘረጋ ይገኛል፡፡
2.5 የገንዘብ ተቋማት፡-
የወረዳው ነዋሪዎች ዘመናዊ የባንክና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎትን ከወረዳው ዋና ከተማ አረካ ውስጥ ከሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት ያገኛሉ፡፡
III. የማህበራዊ አገልግሎት
3.1 ጤና
3.2 ትምህርት
መዋዕለ ሕጻናት ት/ቤት --------------------------- 12
አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-4ኛ ክፍል) -------------- 4
አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-8ኛ ክፍል) -------------- 35
ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (9-10ኛ ክፍል) ------------ 3
መሰናዶ (11-12ኛ ክፍል) -------------------------- 2
IV. በመስኖ የሚለማ የእርሻ መሬት ሁኔታ
በወረዳው ውስጥ 3 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ በመሆናቸው የአከባቢው አርሶ አደር ተጠቃሚ ሲሆን ለአብነት ወይቦ መስኖ በማጣላ ሂምቤቾ ቀበሌ (95 ሄ/ር)፣ ሶኬ መስኖ በጢዮ ሂምቤቾ ቀበሌ (273 ሄ/ር)፣ እና ኢጣና መስኖ በጉሩሞ ኮይሻ ቀበሌ (60 ሄ/ር) የመስኖ ፕሮጀክቶች አገልግሎት እየሰጡ በመሆናቸው ለአከባቢው ማህበረሰብ ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ አንጻር አዎንታዊ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛል፡፡ ከዚሁ በተጨማሪ ወረዳው ካለው የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውኃ አቅርቦት ለአብነት ወንዞች (ወይቦ፣ ጋሞ፣ ሻፋ፣ ሶኬ፣ ቁሌ እና ዎተሬ ወንዞች) ከመኖሩ አንጻር እስካሁን በመስኖ የለማው መሬት መጠን በጣም ዝቅተኛ ከመሆኑም ባሻገር ወረዳው ከፍተኛ ለመስኖ አገልግሎት ሊውል የሚችል የውኃ ፖቴንሻል እንዳለ፣ ከፍተኛ የዝናብ መጠን መኖሩ እና ለም ዐፈር መኖሩ ለእርሻ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡
V. በወረዳው የሚመረቱ ዋና ዋና ምርቶች
51 ዓመታዊ ሰብሎች
በቆሎ፣ ጤፍ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ሽንብራ፣ ገብስ፣ የሥራ ሥር ሰብሎች፣ አትክልት (ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማትም)፣ ቅመማ ቅመም ምርት (ዝንጅብል፣ ዕርድ)፣
5.2 ቋሚ ሰብሎች
ፍራፍሬ (ሙዝ፣ ማንጎ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን)፣ አናናስ፣ እንሰት፣ ቡና፣
VI. ለኢንቨስትመንት የተዘጋጀ መሬት፡-
.ቁ
ለኢንዱስትሪ
ለኮኮብ ሆቴል፣ ለሪል ስቴትና ለማህበራዊ አገልግሎት
ለከተማ ግብርና በሄ/ር
ለገጠር እርሻ ልማት በሄ/ር
1
87.4
------
-----
135 ሄ/ር
ምንጭ፡- የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት
ማሳሰቢያ፡- ለገጠር እርሻ ኢንቨስትመንት የተለዩ ቦታዎችን በተመለከተ በተለያዩ የወረዳው ቀበሌዎች ውስጥ ሰርቨይ ተደርጎ የተለየ 135 ሄ/ር የወል መሬት በሶማሞ ጫሬ እና በዱቦ አከባቢ እንዲሁም በሂምቤቾ ከተማ ለኢንዱስትሪ ዞን ተካልሎ ከሚገኘው መሬት በተጨማሪ በወረዳዉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት አማካይነት በተፋሰስ ሊለሙ የሚችሉ በተለያዩ ቀበሌዎች ተጠንቶ የተካለለው ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሊውል የሚችል መሆኑን ታሳቢ ሊደረግ ይገባል፡፡
VII. ለኢንቨስትመንት ያለው አመቺነት
7.1 ለግብርና
7.2 ለአግሮ ኢንዱስትሪ
7.3 ለማህበራዊ አገልግሎት
የወረዳው የጤና ሽፋን 81.4% ብቻ መሆኑ በተለይም በላቦራቶሪ እና በግል ፋርማሲ ተቋማት ሽፋን ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤
የመዋዕለ ሕጻናት እና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ብዛት ዝቅተኛ መሆኑ እንዲሁም በከፍተኛ የት/ት ተቋማት ወይም ኮሌጆች በወረዳው ውስጥ ያለመኖር ለግል ባለሀብት በመስኩ መሰማራት አመችነቱን ይጠቁማል፡፡
7.4 ለሆቴል፣ ለሪዞርት፣ ለሎጅ፣ ለመዝነኛ ፓርክ እና ቱሪዝም አገልግሎት
7.5 ለማዕድን፣ ኢነርጅ እና ለኮንስትራክሽን ዘርፍ
VIII. የኢንቨስትመንት አማራጭ ዕድሎች
8.1 ግብርና ዘርፍ
8.2 በማህበራዊና በአገልግሎት ዘርፍ
8.3 በኢንዱስትሪ ዘርፍ
የኢንዱስትሪ ፖቴንሻል ሰርቨይ / / ጥናት መሠረት በከተማው ውስጥ
Copyrights 2019. . All Rights Reserved.
Developed by SNNPRS-SITB & SNNPRS-wza