• Call Us
  • +251465512106

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ አስተዳደር

. አጠቃላይ ገጽታ   

የወረዳው ዋና ከተማ ሻንቶ ከዞናችን ርዕሰ መዲና ሶዶ በስተሰሜን በ28 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝና የቆዳ ስፋቱም 165 ካሬ ኪ/ሜትር ሲሆን በ22 የገጠር ቀበሌዎች እና በ2 የማዘጋጃ ቤት ከተሞች የተዋቀረ ነው፡፡ በአስተዳደሩ የሚገኙ የኢንቨስትመንት አማራጮች፤ የማዕድን ሀብት ክምችትና የቱሪስት መስህቦች እንደሚከተለዉ ቀርበዋል፡፡

1.1 ከባህር ወለል ከፍታ             

ከባህር ወለል በላይ ከ1,500 እስከ 2,000 ሜትር ከፍታ ያላቸው የመሬት ገጾች አሉት፡፡

1.2 የአየር ንብረት

የወረዳው አግሮኢኮሎጂን በተመለከተ 100% ወይና ደጋ ነዉ፡፡ የዓመቱ አማካይ የሙቀት መጠን 17.6--20 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ነው፡፡ አማካይ ዓመታዊ የዝናብ መጠን ከ1000 እስከ 1,400 ሚሊ ሜትር ነው፡፡

1.3 ሥነ-ሕዝብ

በ2009 ዓ.ም ከዞኑ ፋ/ኢ/ል/መምሪያ በተገኘው የስታትስቲክስ መረጃ መሠረት የወረዳው አጠቃላይ የሕዝብ ብዛት 140,104 ሲሆን የሕዝብ ጥግግት 723 በካሬ ኪ/ሜትር ነው፡፡

  . የመሠረተ ልማት አቅርቦት ሁኔታ   

2.1 መንገድ

ወረዳው ውስጥ 29 ኪ/ሜትር የጠጠር እና 596.75 ኪ/ሜትር ጥሪጊያ መንገዶች ሲኖሩት በአብዘኛው የወረዳው ቀበሌዎች ከዞንና ከክልል ብሎም ወረዳን ከወረዳ እንዲሁም እያንዳንዱን የገጠር ቀበሌም ጭምር በዋናና በውስጥ ለውስጥ መንገዶች እርስ በእርስ የተገናኘ ነው፡፡

2.2 ስልክ፣ ኢንተርኔት እና የፖስታ አገልግሎት

የሞባይልና የመደበኛ ስልክ አገልግሎት፣ እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎት የሚሰጡ የግል ንግድ ማዕከላት እየተከፈቱ ይገኛሉ፡፡ አንድ የፖስታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በሻንቶ ከተማ ይገኛል፡፡

2.3 መብራት

በወረዳው ውስጥ የሚገኙ የከተማ አከባቢዎች 24 ሰዓት የሃይደሮ ኤሌክትሪክ ኃይል መብራት አገልግሎት ያገኛሉ፡፡

2.4 የመጠጥ ውኃ አቅርቦት

የመጠጥ ውኃ አቅርቦትን በተመለከተ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ የእጅ ጉድጓድ (                                    ) 35፣ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ ጥልቅ ጉድጓድ (                                   ) 80፣ ጥልቅ ጉድጓድ ስርጭት (                       ) 4፣ ምንጭ በቦታው ማጎልበት (           ) 2 ይገኛሉ፡፡ የወረዳው የመጠጥ ውኃ ሽፋን 66.14% ሲሆን በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ችግር ለማቃለል የጥልቅ ጓድጓድ ውኃ አገልግሎት ለመስጠት በተለያዩ ቀበሌዎች መስመር እየተዘረጋ ይገኛል፡፡

2.5 የገንዘብ ተቋማት፡-

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ቪዥን ፈንድ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም፣ ኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም እንዲሁም ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት እየተከፈቱ ይገኛሉ፡፡

   . የማህበራዊ አገልግሎት     

3.1 ጤና

  • ጤና ጣቢያ /             / ------------- 5
  • ጤና ኬላ /           / ------------------ 22
  • የመጀመሪያ ደረጃ ክሊንክ /      / -------- 9 (የግል)  
  • መድኃኒት ቤት /        / --------------- 5 (የመንግስት)
  • መድኃኒት መደብር (           ) ------ 1 (የግል)
  • ላቦራቶሪ ---------------------------------------  5 (የመንግስት)
  • የጤና ሽፋን -----------------------------------  86%

3.2 ትምህርት

መዋዕለ ሕጻናት ት/ቤት --------------------------- 3  

አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-4ኛ ክፍል) -------------- 1

አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-8ኛ ክፍል) -------------- 24

ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (9-10ኛ ክፍል) ------------ 2

መሰናዶ (11-12ኛ ክፍል) --------------------------- 1

  . በመስኖ የሚለማ የእርሻ መሬት ሁኔታ                        

ወረዳው ካለው የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውኃ አቅርቦት ለአብነት ወንዞች (ወዴባ፣ ጋሞ፣ እና ማጥኔ ወንዞች) ከመኖሩ አንጻር እስካሁን በመስኖ የለማ መሬት አለ ለማለት የሚያስደፍር ሁኔታ ባይኖርም ወረዳው ከፍተኛ ለመስኖ አገልግሎት ሊውል የሚችልና በቅርብ ጥልቀት የሚገኝ የከርሰ ምድር ውኃ ፖቴንሻል መኖሩ፣ ከፍተኛ የዝናብ መጠን መኖሩ እና ለም ዐፈር መኖሩ ለእርሻ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡

 

 

 

 . በወረዳው የሚመረቱ ዋና ዋና ምርቶች

5.1 ዓመታዊ ሰብሎች

በቆሎ፣ ጤፍ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ገብስ፣ የሥራ ሥር ሰብሎች (ድቡልቡል ድንች፣ የወላይታ ድንች፣ ስኳር ድንች፣ ጎዳሬ)፣ አትክልት (ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማትም)፣ ቅመማ ቅመም ምርት (በርበሬ)፣ ሸንኮራ አገዳ፣

5.2 ቋሚ ሰብሎች

ፍራፍሬ (ሙዝ፣ ማንጎ፣ አቮካዶ)፣ እንሰት፣ ቡና፣

  . ለኢንቨስትመንት የተዘጋጀ መሬት

ተ.

ለኢንዱስትሪ በሄ/ር  

ለንግድ፣ ለአገልግሎት፣  በሄ/ር

ለከተማ ግብርና በሄ/

ለማህበራዊ አገልግሎት በሄ/ር  

1

50

7.54

29.12

1.83

     ምንጭ፡- ሻንቶ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት

ማሳሰቢያ፡- ከወረዳው ከተማ ልማት ጽ/ቤት እና ከሻንቶ ማዘጋጃ ቤት በተገኘው መረጃ መሠረት ከ88 ሄ/ር በላይ መሬት ለተለያዩ አገልግሎቶች በከተማው መሠረታዊ ፕላን መሠረት የተዘጋጀ መሆኑን ታሳቢ ሊደረግ ይገባል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ወረዳው በዞናችንም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ በህዝብ ጥግግት ከፍተኛ በመሆን የመጀመሪያው ደረጃ የያዘ ስለሆነ አርሶ አደሩ ገበያ ተኮር የሆኑ ምርቶች ምርታማነትን በማሳደግና በተፋሰስ የለሙ ቦታዎችን በአግባቡ ለአትክልትና ፍራፍሬ፣ ለንብ ማነብ፣ ለበግ ማሞከት፣ ለእንስሳት ዕርባታና ድለባ፣ እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን በበቂ ሁኔታ ለማቅረብ ያሉትን ምቹ ሁኔታዎችን መጠቀም ያስፈልጋል፡፡

    . ለኢንቨስትመንት ያለው አመቺነት

7.1 ለግብርና          

  • በወረዳው ውስጥ ዓመቱን ሙሉ የማይደርቁ ወንዞች በመኖራቸው እንዲሁም በተፋሰስ የለሙና የተካለሉ ሰፊ ቦታዎች ያሉት በመሆኑ በንብ ማነብ፣ በበሬ ድለባ፣ በበግ ማሞከት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣ በዘመናዊ እንሰሳት ዕርባታ፣ ለዶሮ ዕርባታ ለማካሄድ ምቹ መሆኗ፣
  • በልማት ሥራ ላይ ለማዋል በቂ የሰው ኃይል /የተማረ እና የጉልበት/ መኖሩ፣
  • በለሙ ተፋሰሶች እና በአርሶ አደር ማሳ የተሻሻለ መኖ፣ ምጥን መኖ፣ የተለያዩ የሰብል ተረፈ ምርቶች፣ የተፈጥሮ ግጦሽ መኖ አቅርቦት መኖሩ፤
  • ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠን ከፍተኛ መሆኑ፣
  • የተሻሻለ የእንስሳት ዝሪያ እየተስፋፋ መሆኑ (በሰው ሰራሽ ዘዴ በማዳቀል)፤
  • ከፍተኛ የሀገረሰብና የተሻሻለ የበግ እና የዶሮ አቅርቦት መኖሩ፤
  • ከፍተኛ የወተት ምርት፣ የወተት እና ተዋጽኦ ምርት ፍላጎት እንዲሁም የመስሪያ ቦታና የመሠረተ ልማት አቅርቦት መኖሩ ለኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ የተመቻቹ ሁኔታዎች ናቸው፡፡

7.2 ለአግሮ ኢንዱስትሪ

  • ከአርሶ አደሩ የሚገኙትን የግብርና ምርቶችን (በአውትግራውር ከአርሶ አደሩ ጋር ትስስር በመፍጠር) በጥሬ ዕቃነት ተጠቅሞ በማቀነባበር እስከ ውጪ ገበያ ድረስ ለሚያቀርቡ ባለሀብቶች መሬቱ አመቺነት ያለው በመሆኑ ያለውጣውርድ ማግኘት ይቻላል፤
  • ለተለያዩ ፋብሪካዎች በጥሬ ዕቃነት ሊያገለግሉ የሚችሉ የግብርና ምርቶች የሆኑ እንደ አቮካዶ፣ ቡና፣ ድቡልቡል ድንች፣ ስኳር ድንች፣ ሙዝ፣ ቦሎቄ እና እንስሳት ሀብት በቅርብ መገኘታቸዉ፤
  • የወተት እና የወተት ተዋጽኦ ለማቀነባበር ከፍተኛ የወተት ምርት መኖሩ፣
  • የሥጋ ምርት (የዳልጋ ከብት፣ የዶሮ፣ ወዘተ) ለማቀነባበር የተሻሻሉ ዝሪያ፣ የተዳቀሉ እና የሀገረሰብ ዘር አቅርቦት መኖሩ፣
  • ምጥን የከብቶች መኖ ለማዘጋጀት በቂ የግብዓት አቅርቦት እና ከፍተኛ የምርት ፍላጎት መኖሩ፤ በአሁኑ ወቅት በተፋሰስ በለሙ ቦታዎች በስፋት እየተመረተ በመሆኑ እንዲሁም በቀላሉ ሊለማ የሚችልና በቂ የተዘጋጀ ቦታ መኖሩ፤   

7.3 ለማህበራዊ አገልግሎት

የወረዳው የጤና ሽፋን 86% ብቻ መሆኑ በተለይም በላቦራቶሪ እና በግል ፋርማሲ ተቋማት ሽፋን ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤

የመዋዕለ ሕጻናት እና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ብዛት ዝቅተኛ መሆኑ እንዲሁም በከፍተኛ የት/ት ተቋማት ወይም ኮሌጆች በወረዳው ውስጥ ያለመኖር ለግል ባለሀብት በመስኩ መሰማራት አመችነቱን ይጠቁማል፡፡

7.4 ለሆቴል፣ ለሪዞርት፣ ለሎጅ፣ ለመዝነኛ ፓርክ እና ቱሪዝም አገልግሎት

  • በወረዳው ዋና ከተማም ሆነ በሌሎች አከባቢዎች ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል፣ ፔንሲዮን እና የመዝነኛ ማዕከላት ያለመኖሩ በዘርፉ የገበያ ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤
  • አዋጁዋ ዛንባ (ታርካዊ ዘንባባ) 1890ዎቹ መጀመሪያ አከባቢ በአጼ ምኒሊክ እና በካዎ ጦና የጦር ሠራዊት መካከል ያለውን ፍልሚያ ለማሸነፍ የወላይታ ህዝብ ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ ተሰብስበው የመከሩበትና የተወያዩበት ቦታ በሻንቶ ከተማ ውስጥ በመኖሩ፤
  • ታሪካዊ የጦር አውድማዎች ለአብነት ባንኤ ቶርቁዋ፣ አልቤ ቦሁዋ፣ ወዘተ
  • ዕድሜ-ጠገብ እና ታሪካዊ የሆኑ የዋርካ እንጨቶች ለአብነት የጋሜ ካፈቾ ወላ (ከ18ኛው ክ/ዘመን ጀምሮ የቆየ)፣
  • ታሪካዊ የሆኑ ዋሻዎች ለአብነት አልቤ ቦሁዋ (በደምባ ጋሌ ቀበሌ)፣ እንዲሁም በወረዳው ውስጥ ሌሎች ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህቦች ስላሉ ቱሪስት የመሳብ አቅም ከፍተኛ ስለሆነ እንዲሁም ለዘርፉ ኢንቨስትመንት በቂ የተዘጋጀ በመሆኑ ባለሃብቱ ቢሠማራበት አዋጭ ነዉ፡፡

 7.5 ለማዕድን፣ ኢነርጅ እና ለኮንስትራክሽን ዘርፍ

  • ለኮንስትራክሽን የሚያገለግሉ ጥሬ ዕቃዎች በአከባቢዉ መገኘታቸዉ፣ ነጭ ድንጋይ እና ጥቁር ድንጋይ (በኦሎላ፣ በጉድቾ፣ ሱቄ ባቃላ ቀበሌ እና በሌሎች ቀበሌዎች)፣ ሴሌክቲድ ማቴሪያል የመሳሰሉት በከፍተኛ መጠን መኖሩ፤

    . የኢንቨስትመንት አማራጭ ዕድሎች

8.1 ግብርና ዘርፍ

  • በግ ማርባትና ማሞከት፣
  • በዶሮ ዕርባታና እንቁላል ምርት፣
  • አትክልትና ፍራፍሬ ልማት (ማንጎ፣ አቦካዶ፣ ሙዝ)፣
  • ቅመማ ቅመም (በርበሬ፣ ቃሪያ) ልማት፣
  • የወተትና ሥጋ ከብት ማርባትና የዳልጋ ከብት ማድለብ፣
  • የእንስሳት መኖ ዘር ማባዛትና ማልማት፣
  • የአገዳ ሰብሎችን ማምረት፣
  • ቡና እና ሌሎች ገበያ ተኮር ሰብሎችን ማምረት፣
  • የሐር ትል ማርባት፣
  • የእንጆሪ ተክል ማልማት፣

8.2 በማህበራዊና በአገልግሎት ዘርፍ

  • በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ከካፌ እስከ ባለኮከብ ሆቴል
  • ነዳጅ ማደያዎች እና ከፍተኛ ጋራዥ፣
  • ሱፐር ማርኬት /የገበያ ማዕከላት፣ ሪል ስቴት/ ገንብቶ ማከራየት፣
  • ላውንዴሪ አገልግሎት፣
  • የጅምላ ንግድ ማከፋፈያ፣
  • በትምህርት ዘርፍ ከመዋዕለ ህፃናት እስከ ኮሌጅ፤
  • በጤና ዘርፍ በክሊኒክ፣ ላቦራቶሪ፣ ፋርማሲ፣ በእንስሳት ህክምና ማዕከላት፣
  • በመዝነኛ አገልግሎት ዘርፍ፡- ሲኒማ ቤቶች፣ ፊልምና ቲያትር ቤቶች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ጂም ቤቶች እና ሌሎች

8.3 በኢንዱስትሪ ዘርፍ

 የኢንዱስትሪ ፖቴንሻል ሰርቨይ /   / ጥናት መሠረት በከተማው ውስጥ

  • ለአትክልትና ፍራፍሬ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣
  • የእንስሳት መኖ ዘር ማባዣ፣ ማቀነባበሪያና ማሸጊያ ፋብሪካ፣
  • በቡና መፈልፈያና ማቀነባበሪያ፣
  • የሐር ምርት ማቀነባበር፣
  • ድቡልቡል ድንች ማቀነባበር፣
  • ለምግብና ምግብ ውጤቶች ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣
  • ለሥጋና የሥጋ ውጤቶች ማቀነባበሪያ፣
  • የወተትና የወተት ውጤቶች ማቀነባበሪያ፣

ብሎኬት እና ሌሎች የግንባታ ዕቃዎችን ማምረት፣