ደስታና ሐዘን የሰው ልጅ የሕይወት ገጽታዎች ሲሆኑ ገጽታዎቹ ከሥፍራ ሥፍራ ከጊዜ ወደ ጊዜ ልዩነት ይስተዋልባቸዋል፡፡
የወላይታ ብሔር ሀዘን የሚገልጽባቸው የተለያዩ የለቅሶ ሥርዓት ሂደቶችና አውዶች አሉት፡፡ እነዚህም፡- ቃሬታ (Qaretaa)፣ ባሊያ(baliyaa)፣ ፒቱዋ (pituwaa) እና ጋባ (gaabaa) ተብለው ይታወቃሉ፡፡ ለባህላዊ ለቅሶ ሥርዓት አፈጻጸም የሚያስፈልጉትን የሙዚቃ መሣሪያዎችና አልባሳት የሚከተሉት ናቸው፡፡
በነባሩ ባህል እንደቅርበታቸው በፈረስ ላይ ኃዘንተኞች ራሳቸውን በአለንጋ ሲገርፉ፣ እግረኞች በመፍረጥ (hirxxiya) እየወደቁ ኃዘናቸውን የሚገልጹ ሲሆን ሴቶች (shaashshaa) “ሻሻ” የሚባል ሳር እና በቆንጥር ፊታቸውን እየቧጨሩ፣ ፈረሰኞች፣ እግረኛ ወንዶችና ሴቶች በመሆን በቅደም ተከተል እየተመላለሱ ያለቅሳሉ፡፡ የባሊያ ተሳታፊዎች አስክሬኑ ከተቀበረ በኋላ ነው ምግብ የሚመገቡት፡፡ በባህሉ አስክሬን ሳይቀበር ለቀስተኛ ምግብ አይመገብምና፡፡ በዚህን ወቅት ሟቹ በአከባቢው ነዋሪ ከሆነ በቤተዘመድ የቀብር ቦታ “በመካና” ይቀበራል፡፡ ሟቹ ከሌላ አከባቢ በሥራ ምክንያት ወይም በሌላ የመጣ ከሆነ “በጉታራ” ይቀበራል፡፡
ከቀብር መልስ ለአማች፣ ለቤተዘመድ፣ ለጃላና ለአጃቢዎቻቸው አስከትለው የሟች እድሮችና ጎረቤቶች መስተንግዶ ያደርጋሉ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ንፍሮ፣ ቂጣ፣ በቅጠል ቡና እና በፍሬ ቡና መስተንግዶ የሚደረግ ሲሆን ሟቹና ቤተሰቡ ታዋቂ ከሆነ በሬ ታርዶ የስጋ መስተንግዶ ይደረጋል፡፡ ለቀስተኞች እንደየቅርበታቸው ለሟች ቤተሰብ የጭነት እህል (caanaa) ወይም ብር (yessaa) በማስተዛዘኛነት (ለማጽናኛነት) ይሰጣሉ፡፡ ከዚያም በኋላ “Hayquwa haysse otto” እያሉ መርቀው ይሄዳሉ፡፡ ማለትም ሞት እይንካችሁ፤ ዳግም አይምጣባችሁ ብለው መርቀው ይሄዳሉ፡፡
pittuwa (ጠረጋው ቀን)፡- ሥርዓቱ ከባሊያ ፍጻሜ በኋላ ለወንድ አራተኛ ቀን ለሴት ሦስተኛ ቀን የሚደረግ ሥነ-ሥርዓት ሲሆን በዕለቱ የሟች ቤተሰብ ዕድርተኞ የሚሰበሰቡ ሲሆን በሂደቱ ሴቶች የሟቹን ቤትና ግቢ ያጸዳሉ፡፡ ወንዶች ደግሞ ለቀብር ቀን የተሠራ ዳስ (ድንኳን) የሚያነሱ ሲሆን ሴቶች ከየቤታቸው ያመጡትን ቆጮ፣ ንፍሮ፣ ቂጣ፣ እንጀራ፣ ቡና በማስተናገድ ወደየቤታቸው ይመለሳሉ፡፡
“Gaabaa” (ማሳረጊያ)
“ጋባ” (ማሳረጊያ)፡- በባህሉ ከባሊያ አራት ቀን በኋላ ረዥም ቀጭን ለጋ እንጨት ተቆርጦ ይላጥና በሟች ቤተሰብ በራፍ ላይ ይደረጋል፡፡ ለቅሶው ይቁም ለቀስተኛ (ኃዘንተኛ) አይምጣ የቤቱም አያልቅስ እንደማለት ነው፡፡
ከባሊያ ፍጻሚ አራት ቀን በኋላ የሟች ቤተሰብ እንዳያዝን ቢከለከሉም እስከ አንድ ዓመት ድረስ ሀዘንተኛ እንደሆኑ የሟች ቤተዘመድ ሴቶች ፀጉራቸውን ሳይላጩ ወንዶች ሳይቆረጡ፣ ወደ መዝናኛ ሥፍራዎች አይሄዱም፤ ገበያም አይወጡም፡፡ ሟች የሞተው በክብር በዓላት ጊዜ ከሆነ ክብረ በዓሉን በኃዘን ያሳልፋሉ፡፡ ለበዓሉ ጎረቤት ከየቤታቸው አምጥተው ያበላሉ እንጂ ቤተሰቡ አያርድም፡፡
የሐዘን እንጉርጉሮ (Buuttuluwaa)
በባህሉ ለሟቹ መታሰቢያ የሀዘን እንጉርጉሮ (Buuttuluwaa) በጾታ፣ በዕድሜ እና ለአከባቢው ባበረከተው አስተዋጽኦ መጠን ይለያያል፡፡
ወጣት ሴት ከሞተች
ቴሬና ቃውኤ
Teerenna qa’uea
Yelaga mulssee… እያሉ የልጅቱን ወጣትነትና ገና መሆኑዋን እየገለጹ በዜማ ያለቅሳሉ፡፡
Makki makki naagiyore neyyoo… yeeho
Maana wodiyan aggiyaare neyyo yeeho
ትርጉሙ፡- ተሰናድቶ የሚጠብቅሽን ሳትቋደሽ የሞትሽብን እያሉ በመሪሪ ሐዘን ያለቅሳሉ፡፡
Godiya goojjaamiya lil’iyaaro
Lil’aa lil’ada ayiyaaro
Balttette bayiree
Goojjaame lill’ee
ትርጓሜውም የባልቴቶች ሁሉ ታላቅ….”
Olawu odolchchaa kooriyaaro
Banggaa buraatuwa shinqqiyaro
Ojonchcha gassa gochchiyaro ጀግናው ለጦርነት ሲሄድና ሲመጣ የምታደርግለትን የተባባሪነትና የተሳታፊነት ሚናዋን ይገልጻሉ፡፡
Onakko nayi xinqqay meqiis
Onakko nayi woyishshay woddiis
Ayye laggee aayye laggee
Aayye miyyee aayye miyyee
ዋይ ጓደኛ ዋይ ወገን እንደማለት ነው፡፡
Dabaabawu daaddaara
Allagawu ayifiyara
Onakko nay daama gaammoy
Daama gaammoy bazzo hasoy
የእገሌ ልጅ እምቦሶ .. የእገሌ ልጅ ዘንዶ እያሉ ጉብዝናውን ይገልጻሉ፡፡
Ho solo … ዜማ አዝማቹ (ተቀባዩ የሟች ግዳይ እየገለጸ ጀግንነቱን በመዘከር ያለቅሳላቸዋል፡፡
Tobbe ba kombbee ba
Zaallay za’iis wolay woddiis.… አማካሪያችንን ነጠቀብን፤ አለታችን ተሰነጠቀ--- ወደቀ እያሉ የቅርስነት ፋይዳውን እየገለጹ ያለቅሳሉ፡፡
Deriyappe deexuwa nawu
Kawaappe kaaluwa na’awu
የንጉሥ ታናሽ ልጅ እያሉ ስልጣኑን እያሞካሹ ያለቅሳሉ፡፡
Erawu Eessawu koottay me’iis.
Garuwawun garxxiya xam’’ay
የእውቀት ባለቤት ተሰበረ፣ ለሩቅ የምንልከው ሰው አጣን እንደማለት ነው፡፡
Miizzaa deegaraa daaliyaga
Biraa miilooniya shiishshiya
Aayye galddee
Aayye mulssee
የሀዘን እንጉርጉሮዎቹ ወንድ ለቀስተኞች በሁለት ተከፋፍለው የሚያንጎራጉሩት ሲሆን ለባሊያ ድምቀት ይሰጣሉ፤ የሟቹን ገድሎችና አስተዋጽኦ በማስታወስ ልዩ የሀዘን ድባብ ይፈጥራሉ፡፡ ሌላው ደግሞ ጭቃሹም ከሞተ አስክሬኑ ሲነሳ የሚዘመው
Hoo hosttagesaallagee
Dannattee darottette. ያባልለታል፡፡
በለቀስተኞቹ (Buttuluwaa) በቡድን የሚዜም ሲሆን በባህሉ የሟች ቤተዘመዶች የሟቹን ውሎ፣ ገድል፣ አስተዋጽኦ፣ ቁመና፣ የዘር ሐረግ … በዜማዊ ቅላጼ (zilaassaa) እያንጎራጎሩ ሐዘናቸውን ይገልጻሉ፡፡
በለቅሶው ወቅት የለቅሶ አውድ የሟች ቤተዘመዶች ልብሳቸውን ገልብጠው ይለብሳሉ፡፡
የቤቱ አባወራ ከሞተ ሚስት የሟቹን ሱሪ ወደ ትከሻዋ ጣል ታደርጋለች፣ እህት፣ አክስት፣ እና የልጅ ሚስት ካሉ በነጠላቸው ላይ “ዋሩዋ” (ማቅ) ይደርባሉ፡፡ ሟች በጦርነትና በአደን ጊዜ ጀብድ ግዳይ የጣለ ከሆነ የሟች ባለቤትና ዘመዶች “baalliya” በጸጉራቸው ይሰካሉ፡፡
የጦር መሪ ከሞተ ለቅሶውን የሚያደምቁ ቀረርቶ የሚችሉ ሁለት ሰዎች የአንበሳ፣ የነብር ቆዳና ድንጉዛ (ሀዲያ) ደርበው ጎፈር በራሳቸው በመድፋና አድርገው keexaa woykko guchchiya ላባ አጊጤው በቀረርቶ መልክ ሙሾ እያወረዱ ያለቅሳሉ፡፡
ሟች ጀግና ከሆነ ፈረስ በጌጤኛ አልባሳትና ጌጣጌጦች ተውቦ በጭንቅላቱ ሁለት ላባዎች ሰክተውለት ፈረሱ ላይ በመሆንና ጦር በመያዝ የሟቹን ጀግንነት ይዘክራሉ፡፡
ሟች ባህላዊ ዳኛ ወይም ሹም ከሆነ በዳኝነቱ ጊዜ ወይም በሹመቱ ጊዜ ያገኛቸውን ካባዎች ልጆቹ አልያም ወንድሞቹ አሊያም የቅርብ ዘመዶቹ ይደርባሉ፡፡ በወቅቱ የአለባበስ ሥርዓቶች ሟቹን ከመዘከር ጎን ለጎን ለለቅሶ ስርዓቱ ጉልህ ድምቀት ይሰጣሉ፡፡
የባህላዊ ለቅሶ አውድ የሙዚቃ መሳሪያዎች
ለወላይታ የለቅሶ ስነ ስርዓት “ባሊያ” ወይም ቀብር ቀን የሚደረጉ buttuluwaa እና zilassaa ማጀቢያ የምትና የትንፋሽ የሙዚቃ መሣሪያዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ እነዚህም
በወላይታ ብሔር በባህላዊ ወግና ስርዓት የሚደረገው የለቅሶ ስርዓቶች በጊዜ ሂደት እየከሰሙ ስለመጡ በጽሑፍና በምስል ተቀርጸው ቢቀመጡ ቀጣዩ ትውልድ የራሱን ባህልና ቅርስ እንደይረሳ የራሱ አስተዋጽኦ ይኖረዋል እንላለን፡፡
Copyrights 2019. . All Rights Reserved.
Developed by SNNPRS-SITB & SNNPRS-wza