የሰው ልጅ በዕለት ተዕለት ኑሮው ለሚጠቀምባቸው ቁሳቁስ፣ ለእንስሳት፣ ለዕጽዋት፣ ለሰዎች ለቦታዎች ወዘተ… ስያሜን ይሰጣል፡፡ ይህም አንድን ነገር ከሌላው ለመለየት፣ ሀዘኑንና ደስታውን፣ ድሉንና ሽንፈቱን ለመግለጽ በስያሜዎች ይጠቀማል፡፡ ጥንት ሀሳብን በጽሁፍ መግለጽ ባልተለመደበት ጊዜ አንድ ማሕበረሰብ ባህሉን፣ ወጉን፣ እምነቱንና ታሪኩን በቦታ እና በሚወልዷቸው ልጆች ስም አማካኝነት ይገልጻል፡፡ በመሆኑም ልጅ ከወለዱ በኋላ ለልጃቸው ስም ለመስጠት የተለያዩ አጋጣሚዎችን ይጠቀማሉ፡፡ ከእነዚህም የተለያዩ ወቅቶች፡- የጦርነት፣ የደስታ፣ የሐዘን፣ የጥጋብ እንዲሁም በተለያዩ ቦታዎች መለኮታዊ አስተሳሰቦች እና የጀግንነት ሁኔታዎች በተለምዶ የሚታዩ ዋና ዋና ከስም አወጣጥ ጋር የሚቆራኙ ናቸው፡፡
በወላይታ ባህል፣ ለሚወለደው ልጅ ስያሜ መስጠት እንደ ሌላው የዓለም ሕዝብ የተለመደና የራሱ የሆነ የብሔሩ ባህላዊ የስም አወጣጥ ያለው ሲሆን በባህሉ መሠረት ሰዎች የወለዷቸውን ሕፃናት ሲሰይሙ ከሁኔታዎች ጋር እያቆራኙ እንደሚሰይሙ እንመለከታለን፡፡
የአሠያየም ሥርዓት
1. የመጀመሪያ ሆሄያትን በማመሣሰል መሠየም
በወላይታ ሕዝብ ዘንድ አንድ ሰው ሲጠራም ሆነ ስሙ ሲጻፍ የአባትን ስም አስቀድሞ ነው፡፡ ይህ የአሰያየም ሂደት በራሱ ደግሞ ሌላ የአጠራር ሁኔታን የሚፈጥር ነው፡፡ በዚሁ የአሰያየም ሁኔታ የልጁ እና የአባቱ ስም የመጀመሪያ ሆሄያት ተመሣሳይ የሚሆኑበትን ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ለምሳሌ፡- የአባትዬው ስም ጋንታ (Gantta) ከሆነ የልጁ ስም ጋጋ (Gaagga) ወይንም (Gallaso) ጋላሶ ይሆናል ማለት ነው፡፡ አጠራሩም (Gantta Gaaga) ተብሎ ነው፡፡
ለአብነት የተወሰነውን እንመልከት
ጾታ
የአያት ስም
የአባት ስም
የልጅ ስም
ወንድ፡
መዳልቾ
መና
ማንዳዬ
Madalchcho
Mana
Mandoye
ሴት፡-
ዎዳጆ
ዎጋሶ
ዎይዛሬ
Wodaajo
Wogaaso
Woyizaree
ከላይ የተጠቀሰው የመጀመሪያ ፊደላት መመሳሰል በአባት ብቻ የሚታይ ሳይሆን አንዳንድ ጊዜ ለእናት ስምም አስመስሎ የመሰየም ባህሉ ይዘወትራል፡፡
የተወለደበትን ዕለት ምክንያት በማድረግ የመሰየም ሁኔታ
አንድ ሕጻን ሲወለድ ስም ለመሰየም የወላይታ ሕዝብ ብዙም የስም ፍለጋ ወዲህ ወዲያ አይልም፡፡ ምክንያቱም የተለያዩ አጋጣሚዎች ለወላጆቿ ትውስታ አላቸውና በሁኔታዎች ተደግፈው የመሰየም ባህል አሏቸው፡፡ በዚሁ የተወለደበትን(ችበትን) የቀኑን ስም እንደዋቢ አድርገው የመሰየም ሁኔታ በአብዛኛው ይስተዋላል፡፡ ይህም ከሰኞ እስከ እሁድ ያሉትን የሳምንት ቀናት በወላይታ የየራሳቸው ስም ስላላቸው ስም ለመሰየም አይቸግራቸውም፡፡ ይህንንም በሚከተለው ምሳሌ እንመለከታለን፡፡
ተ.ቁ
የዕለቱ ስም
ስሞች
ለወንድ
ለሴት
1
እሁድ woggaa
Woggaa(ወጋ)Wogaaso (ወጋሶ)
Woggaree(ወጋሬ), Ayyaanee (አያኔ)
2
ሰኞ Saynno Shagga
Saynno(ሰኞ),Borooda (ቦሮዳ)
Saynne (ሳይኔ)
3
ማክሰኞ Ciishshaa
Ciishshaa (ጭሻ)
Ciishshee (ጭሼ)
4
ረቡዕ Wollila
Tufaa(ቱፋ),Oroobaa (ኦሮባ)
5
ሐሙስ Shaaga
Anjjaa(አንጃ),Shaagaa (ሻጋ)
Shaagee(ሻጌ), Anjjoore(አንጆሬ)
6
ዓርብ Bizza
Tuqaa(ቱቃ) Arbaa(ዓርባ)
Arbbee (አርቤ)
7
ቅዳሜ Qeeraa
Giyaa (ጊያ)
አንድ ሕፃን ሲወለድ የተወለደበት ጊዜ በዕለቱ ጥዋት፣ እኩለ ቀን፣ ከሰዓት ማታ ወይም እኩለ ሌሊት ቢሆን ይህንን ጊዜ በማስመልከት የመሰየም ባህል አለ፡፡ ይህም በሚቀጥለው ምሳሌ ተቀምጧል፡፡
የተወለደበት ጊዜ
ስያሜዎች
ጠዋት
Wontta(ዎንታ), Bakkaalo(ባካሎ) Dolaa(ዶላ)
ማላዶ(Maalladee)
እኩለ ቀን
Seeta(ሴታ) Gallasso(ጋላሶ)
ካዎቴ (kawotee)
ከሰዓት በኋላ
ላንኮ(Lankoo) ላንካ (Lankkaa)
ላንካሬ (Lankaree)
ሌላው በወላይታ ሕዝብ ዘንድ የተለመደው በባህሉ አንድ ሕጻን ሲወለድ ከተወለደበት ወቅት ጋር በማገናዘብ የህጻኑን ስም የመሰየም ሁኔታ ነው፡፡ በአመት ውስጥ ያሉ አራት ወቅቶችን በማገናዘብ ነው ይህን የሚያደርጉት፡፡ አንድ ሕጻን ከእነዚህ መካከል በአንደኛው ጊዜ ቢወለድ ከዚያው ከተወለደበት ወቅትና ሁኔታ ጋር በማገናዘብ የመጠሪያ ስም ያወጡለታል፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዘው የሚሠየሙ ስሞችን በከፊል አንመልከት፡፡
በልግ (Badhdheesa)
Badhdheeso, ባዴሶ Saphpheero (ሳጶ)
Badhdheere(ባዴሳ), Dubbee(ዱቤ)
ክረምት Balgguwa
Iroo(እሮ), Caree(ጫሬ), Balggoo(ባልጎ), Shaara(ሻራ)
Iree(ኢሬ), Calalee(ጫላሌ), Gubbanee(ጉባኔ)
በጋ Boniyaa
Gombillo, Bonaa
Bonee (ቦኔ)
ፀደይ Ofinttaa
Illilloo(እልሎ), Pinttaa(ፕንታ), Booqalsoo(ቦቃልሶ)
Booqalssee(ቦቃልሶ), Illilee(እልሌ)
5.ከዘመኑ ክስተትና ሁኔታ ጋር በማገናዘብ መሰዬም
በማህበረሰቡ ዘንድ የተለመደውና ከሁኔታዎችና ከወቅቱ ክስተት ጋር አገናዝቦ የመሰየሙ ሁኔታ ለህዝቡ ልዩ ትኩረትና በሕይወታቸው ደግሞ እንደ አንድ ትውስታ ፈጥረው የሚያልፉ ክስተቶችን በማካተት ይሰይማሉ፡፡ ይህም አንድ ሕጻን በሚወለድበት ዘመን ጠቅላላ በዓመቱ ውስጥ ወይም ጥቂት ዓመታት ውስጥ የተከሰቱትን ጉልህ ክስተቶች፣ ያሉና የሆኑ ሁኔታዎችን ከልጁ ውልደት ጋር በማገናዘብ በዘመኑ ጥጋብ፣ ረሃብ፣ ጦርነት፣ መኣት፣ ምርት፣ ዝናብ፣ መብረቅ፣ ድርቅ፣ ወዘተ… የመሳሰሉት ሁኔታዎች ጎልተው ከታዩ እነዚህን ከሕጻኑ ልደት ጋር በማገናኘት ስም ያወጡለታል፡፡ በተጨማሪም በዚያን ዓመት ውስት የተፈጠሩ የቤተሰብ ወይም የቅርብ ዘመድ ጥል፣ ዕርቅ፣ መለያየት፣ ሹመት፣ ሞት ወዘተ የመሳሰሉ ሁኔታዎች ከተከሰቱ ከተወለደው ሕጻን ጋር በማገናኘት ይሰይማሉ፡፡
ክስተቶች
ጥጋብ (ምቾት) (kaluwaa)
Ishaloo(እሻሎ), Ayyaanoo(አያኖ) konaaso(ኮናሶ), ushachcho(ኡሻቾ)
Mannanee(ማናኔ), Ishalee(እሻሌ)
Bala’’anne(ባልኣኔ), Kumetee(ኩሜቴ)
የምርት ጊዜን በማስመልከት የሚሰየሙት
Dorannaa(ዶራኖ), kumaa(ኩማ), Baraata(ባራታ)
Murutee(ሙሩቴ), Doraannee(ዶራኔ)
Kumetee(ኩሜቴ), Hiraysee(ህራይሴ)
ዝናብ (መብረቅ) ወጨፎ
Iroo(እሮ), Zullaa(ዙላ), Wolqqantta(ዎልቃንቶ)
Iree(እሬ),
ጦርነት
Baassaa(ባሳ), Tooruu(ቶሩ), Minotaa(ምኖታ), Qolchcha(ቆልቻ), Baabisoo(ባብሶ), Kombaaso(ኮምባሶ)
Minotee (ምኖቴ)
እነዚህንና ሌሎች ስሞች የሚሰጡ ሲሆን በዚህ መሠረት የሚሰየሙበት ምክንያትም በወቅቱ የተከሰቱትን ክስተት ክፉም ሆነ ደግ ለማስታወስ ነው፡፡
በወላይታ ባህላዊ፣ ህዝባዊ ወይንም ሃይማኖታዊ በዓል በሚከበርበት ወይም ዕለቱ በተቃረበበት ወቅት ሕጻን ሲወለድ በበዓሉ ስም የሚጠራበት አሊያም ተዛማጅ በሆኑ ስሞች ይጠራል፡፡ ቀጥለው የቀረቡ ምሳሌዎች ይህን እውነታ የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡
በጥንት ዘመንም ሆነ በአሁኑ በቅርብ ርቀት ባሰለፍናቸው ዘመናት አልፎ አልፎ በአንዳንድ ቤተሰብ ውስጥ የተወለዱ ህፃናት በተደጋጋሚ የሚጠራበት ሁኔታ ይከሰታል፡፡ አንዳንድ ጊዜ እንደተወለደ ሲሞት ሌላ ጊዜ ደግሞ በተወለደ በጥቂት ወራት ወይም ዓመታት ውስጥ ገና በህጻንነቱ ይቀጫል፡፡ በዚህ ሁኔታ በተከታታይ የሚወለዱ ህፃናት ሁሉ በሞት ሲነጠቁባቸው ጭንቅ የገባቸው ወላጆች ማምለጫ ፍለጋ ይጀምራሉ፡፡ ለዚህም እንደ ስልት የሚወስዱት ሞት ትቷቸው እንዲያልፍ ለልጆቻቸው የማይረባ፣ የስድብ እና የሚያቋሽሽ ስም በባህሉ ለጊዜውና ቢሆን ሞት የሚፀየፋቸው ስሞች እንዳሉ ይታመናል፡፡ ከእነዚሀ ስሞችም ለአብነት ፡-
ለወንድ፡- Curqqo(ጩርቆ), Darccoo(ዳርጮ), Obbollee(ኦቦሌ) Borkko(ቦርኮ), Manaa(ማና)
ለሴት፡- Sharfee(ሻራፌ), Cinashee(ጭናሾ), Muucee(ሙጨ) Kutushee(ኩቱሸ), Dorsee (ዶርሰ)
በማለት ሞት ለጊዜውም ጊሆን እንዲጸየፋቸው ብለው ይሰይሟቸዋል፡፡
ውበትን፣ ደምግባትንና ቁንጅናን በማስመልከት ይሰይማሉ፡፡ ቆንጆ እና መልከ መልካም ከሆነ(ከሆነች) ይህንን በማስመሰል የሚሰጥ ስም ነው፡፡ ይህንን በሚቀጥለው ምሳሌ እናያለን፡፡
ለወንድ፡- Henjjeero(ሔንጀሮ), Diidoo(ዲዶ), Alleeqo(አለቆ) Bakaalo(ባካሉ), Malsaamo(ማልሳሞ)…
ለሴት፡- Malanchee(ማላንቸ ቆንጅት), Littishe(ልትሼ), Suufare(ሱፋሬ) Walqqasa(ዋልቃሴ), Alleqe(አለቄ) Sildidde(ስልድደ)…
እነዚህ እና ሌሎች በርካታ ቁንጅናን የሚገልጹ ስሞች ይሰየማሉ፡፡
በወላይታ ህዝብ ዘንድ አንዳንድ ጊዜ ሳይወለድ በሚዘገይበት ጊዜ በስለት ወይም በአከባቢው ቋንቋ (shiiqqetaan) ለሚወለዱ ህጻናት እንደሚከተለው ስም ይወጣላቸዋል፡፡
ለወንድ፡- Gam’’a, yaanaa, Anjjulloo, Ukkumoo, Go’’aa…
ለሴት፡- Anjjullee, Ukkumee, Laamotee, Imotee, Go’’itee…
በማለት እነዚህ ልጆች በስጦታ፣ በካሳ መልክ ከፈጣሪ ዘንድ እንደተሰጡ በመቁጠር ስያሜውን ይሰይማሉ፡፡
በአጠቃላይ ከላይ የተመለከትናቸው እና ሌሎች ያልተጠቀሱ ለምሳሌ ከዝነኛ ስሞች ጋር በማመሳሰል ልጆቻቸው የእነዚያ ስሞች እድል ዓይነት እንዲገጥሟቸው በማለት የሚሰይሙበት፣ ከጠንካራ እና ጉልበታም በሆኑ አራዊት ስም የመሰየም እና ሌሎችም ባህላዊ የሆኑ የስም አሰያየም ሁኔታም በአሁኑ ወቅት እየቀረ እና ተተክቶ እናገኘዋን፡፡ በተለይም ከቅርብ ዘመናት ወዲህ ከመጡ ፖለቲካዊ አስተዳደር ዘይቤዎች ከሃይማኖት እና ከዘመናዊ ትምህርት መስፋፋት ጋር ተያይዞ የተፈጠረው ተጽእኖ ይሰተዋላልና፡፡ ባህሉ በዚሁ መሰረት ተጠንቶ መቀመጡ ለቀጣይ ትውልድ ባህሉን ለማስተላለፍ ያለው ጠቀሜታ የጎላ ነው፡፡
ምንጭ፡-
Copyrights 2019. . All Rights Reserved.
Developed by SNNPRS-SITB & SNNPRS-wza