. አጠቃላይ ገጽታ
የኦፋ ወረዳ ዋና ከተማ ገሱባ ከዞኑ ርዕሰ መዲና ሶዶ በስተምዕራብ በ33 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝና የቆዳ ስፋቱም 385.4 ካሬ ኪ.ሜትር ሲሆን በ22 የገጠር ቀበሌዎች የተዋቀረ ነው፡፡ በአስተዳደሩ የሚገኙ የኢንቨስትመንት አማራጮች፤ የማዕድን ሀብት ክምችትና የቱሪስት መስህቦች እንደሚከተለዉ ቀርበዋል፡፡
1.1 ከባህር ወለል ከፍታ
ከባህር ወለል በላይ ከ501 እስከ 2,900 ሜትር ከፍታ ያላቸው የመሬት ገጾች አሉት፡፡
1.2 የአየር ንብረት
የወረዳው አግሮኢኮሎጂን በተመለከተ 24.4% ቆላ፣ 60.1% ወይና ደጋ እና 15.5% ደጋ ነዉ፡፡ የዓመቱ አማካይ የሙቀት መጠን 17.6--22.5 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ነው፡፡ አማካይ ዓመታዊ የዝናብ መጠን ከ1,400 እስከ 1,600 ሚሊ ሜትር ነው፡፡
1.3 ሥነ-ሕዝብ
በ2009 ዓ.ም ከዞኑ ፋ/ኢ/ል/መምሪያ በተገኘው የስታትስቲክስ መረጃ መሠረት የወረዳው አጠቃላይ የሕዝብ ብዛት 138,427 ሲሆን የሕዝብ ጥግግት 349 በስኳየር ኪ/ሜትር ነው፡፡
. መሠረተ ልማት
2.1 መንገድ
የወረዳውን ዋና ከተማ ገሱባ ከሶዶ-ሳውላ አቋርጦ የሚያልፍ የጠጠር መንገድ የተዘረጋ ሲሆን ደረጃውን የጠበቀ የአስፋልት መንገድ ደረጃ ለማሳደግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ፤ ከዚህም በተጨማሪ 201.5 ኪ/ሜትር የጠጠር እና 453 ኪ/ሜትር ጥሪጊያ መንገድ የተለያዩ የወረዳ ቀበሌዎችን እና አጎራባች ወረዳዎችን እርስ በርስ የሚያገናኝ መንገዶች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
2.2 ስልክ፣ ኢንተርኔት እና የፖስታ አገልግሎት
የሞባይልና የመደበኛ ስልክ አገልግሎት፣ እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎት የሚሰጡ የግል ንግድ ማዕከላት እየተከፈቱ ይገኛሉ፡፡ አንድ የፖስታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በገሱባ ከተማ ይገኛል፡፡
2.3 መብራት
በወረዳው ውስጥ የሚገኙ የከተማ ማዘጋጃ ቤት አስተዳደር አከባቢዎች 24 ሰዓት የሃይደሮ ኤሌክትሪክ ኃይል መብራት አገልግሎት ያገኛሉ፡፡
2.4 የመጠጥ ውኃ አቅርቦት
የመጠጥ ውኃ አቅርቦትን በተመለከተ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ የእጅ ጉድጓድ ( ) 2፣ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ ጥልቅ ጉድጓድ ( ) 29፣ ጥልቅ ጉድጓድ ስርጭት ( ) 3፣ የምንጭ ውኃ ስርጭት ( ) 15፣ ምንጭ ማጎልበት ( ) 58 ይገኛሉ፡፡ የወረዳው የመጠጥ ውኃ ሽፋን 68.56% ሲሆን በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ችግር ለማቃለል የጥልቅ ጓድጓድ ውኃ አገልግሎት ለመስጠት በተለያዩ ቀበሌዎች መስመር እየተዘረጋ ይገኛል፡፡
2.5 የገንዘብ ተቋማት፡-
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም እንዲሁም ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት እየተከፈቱ ይገኛሉ፡፡
. የማህበራዊ አገልግሎት
3.1 ጤና
3.2 ትምህርት
መዋዕለ ሕጻናት ት/ቤት -------------------------- 1
አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-4ኛ ክፍል) -------------- 7
አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-8ኛ ክፍል) -------------- 26
ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (9-10ኛ ክፍል) ------------ 3
መሰናዶ (11-12ኛ ክፍል) --------------------------- 1
የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ፖሊቴክኒክ ----------- 1
. በመስኖ የሚለማ የእርሻ መሬት ሁኔታ
በወረዳው ውስጥ 3 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ በመሆናቸው የአከባቢው አርሶ አደር ተጠቃሚ ሲሆን ለአብነት ቡሻ መስኖ በቡሻ ቀበሌ (200 ሄ/ር)፣ መንኢሳ መስኖ በዳቃያ ቀበሌ (200 ሄ/ር) እና ወዮ መስኖ በጋልዳ ቀበሌ (150 ሄ/ር) የመስኖ ፕሮጀክቶች ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ አልፎ ለሀገርቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡ ይሁን እንጂ ወረዳው ካለው የከርሰምድርና የገጸምድር ውኃ አቅርቦት ለአብነት ወንዞች (መንኢሳ፣ ደሜ እና ጎገራ/ሊንታላ) ከመኖሩ አንጻር እስካሁን በመስኖ የለማው መሬት መጠን በጣም ዝቅተኛ ከመሆኑም ባሻገር ወረዳው ከፍተኛ ለመስኖ አገልግሎት ሊውል የሚችል የውኃ ፖቴንሻል እንዳለ፣ ከፍተኛ የዝናብ መጠን መኖሩ እና ለም ዐፈር መኖሩ ለእርሻ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡
. በወረዳው የሚመረቱ ዋና ዋና ምርቶች
ሀ/ ዓመታዊ ሰብሎች
በቆሎ፣ ጤፍ፣ ሰሊጥ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ቦሎቄ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ሽንብራ፣ ማሾ፣ ለውዝ፣ የሥራ ሥር ሰብሎች፣ ጥጥ፣ አትክልት (ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማትም)፣ ቅመማ ቅመም (አርቲሜዥያ)
ለ/ ቋሚ ሰብሎች
ፍራፍሬ (ሙዝ፣ ማንጎ፣ አፕል፣ አቮካዶ)፣ ካሳቫ፣ ሽፈራው፣ ጃትሮፓ (ቆቦ)፣ እንሰት፣ ቡና፣
. ለኢንቨስትመንት የተዘጋጀ መሬት
ተ.ቁ
ለኢንዱስትሪ
ለንግድ፣ ለአገልግሎት፣ ለሌሎች በሄ/ር
ለከተማ ግብርና በሄ/ር
ለገጠር እርሻ ልማት በሄ/ር
1
50 ሄ/ር
35 ሄ/ር
8
250
ምንጭ፡- ገሱባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ጽ/ቤት
ማሳሰቢያ፡- ለገጠር እርሻ ኢንቨስትመንት የተለዩ ቦታዎችን በተመለከተ በማንቻ ጎገራ ቀበሌ ልዩ ስሙ አጉሜ እና ጉሉዋ በተባለው 200 ሄ/ር እንዲሁም 50 ሄ/ር መሬት ከጃትሮፓ ባዮ ፍዩል የተቀማ እና ሰርቨይ ተደርጎ በኢንቨስትመንት መሬት ባንክ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ከገሱባ ማዘጋጃ ቤት በተገኘው መረጃ መሠረት ከ93 ሄ/ር በላይ መሬት ለተለያዩ አገልግሎቶች በከተማው መሠረታዊ ፕላን መሠረት የተዘጋጀ መሆኑን ታሳቢ ሊደረግ ይገባል፡፡
. ለኢንቨስትመንት ያለው አመቺነት
7.1 ለግብርና
7.2 ለአግሮ ኢንዱስትሪ
7.3 ለማህበራዊ አገልግሎት
የወረዳው የጤና ሽፋን 87.1% ቢሆንም በላቦራቶሪ እና በግል ፋርማሲ ተቋማት ሽፋን ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤
የመዋዕለ ሕጻናት እና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ብዛት ዝቅተኛ መሆኑ እንዲሁም በከፍተኛ የት/ት ተቋማት ወይም ኮሌጆች በወረዳው ውስጥ ያለመኖር ለግል ባለሀብት በመስኩ መሰማራት አመችነቱን ይጠቁማል፡፡
7.4 ለሆቴል፣ ለሪዞርት፣ ለሎጅ፣ ለመዝነኛ ፓርክ እና ቱሪዝም አገልግሎት
7.5 ለማዕድን፣ ኢነርጂ እና ለኮንስትራክሽን ዘርፍ
. የኢንቨስትመንት አማራጭ ዕድሎች
8.1 ግብርና ዘርፍ
8.2 በማህበራዊና በአገልግሎት ዘርፍ
8.3 በኢንዱስትሪ ዘርፍ፡- የኢንዱስትሪ ፖቴንሻል ሰርቨይ / / ጥናት መሠረት በከተማው ውስጥ
Copyrights 2019. . All Rights Reserved.
Developed by SNNPRS-SITB & SNNPRS-wza