• Call Us
  • +251465512106

የቦሎሶ ቦምቤ ወረዳ አስተዳደር

 አጠቃላይ ገጽታ

የቦሎሶ ቦምቤ ወረዳ ዋና ከተማ ቦምቤ ከዞኑ ርዕሰ መዲና ሶዶ በስተሰሜን ምዕራብ በ56 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝና የቆዳ ስፋቱም 272.2 ካሬ ኪሜትር ሲሆን በ17 የገጠር ቀበሌዎች እና በሁለት የማዘጋጃ ቤት ከተሞች (ቦምቤ እና ሞሌ ማዘጋጃ ቤት) የተዋቀረ ነው፡፡ በአስተዳደሩ የሚገኙ የኢንቨስትሜንት አማራጮች፤ የማዕድን ሀብት ክምችትና የቱሪስት መስህቦች እንደሚከተለዉ ቀርበዋል፡፡

1.1 ከባህር ወለል ከፍታ

ከባህር ወለል በላይ ከ1,500 እስከ 2,5000 ሜትር ከፍታ ያላቸው የመሬት ገጾች አሉት፡፡

1.2 የአየር ንብረት

የወረዳው አግሮኢኮሎጂን በተመለከተ 40% ቆላ፣ 45% ወይና ደጋ እና 15% ደጋ ነዉ፡፡ የዓመቱ አማካይ የሙቀት መጠን 12.6--25 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ነው፡፡ አማካይ ዓመታዊ የዝናብ መጠን ከ1,200 እስከ 1,600 ሚሊ ሜትር ነው፡፡

1.3 ሥነ-ሕዝብ

በ2009 ዓ.ም ከዞኑ ፋ/ኢ/ል/መምሪያ በተገኘው የስታትስቲክስ መረጃ መሠረት የወረዳው አጠቃላይ የሕዝብ ብዛት 116,226 ሲሆን የሕዝብ ጥግግት 415 በስኳየር ኪ/ሜትር ነው፡፡

  . የመሠረተ ልማት አቅርቦት ሁኔታ

2.1 መንገድ

የወረዳውን ዋና ከተማ ቦምቤን ከአረካ ከተማ እና ከሞሌ መንኢሳ የሚያገናኝ የጠጠር መንገድ የተዘረጋ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ 70.4 ኪ/ሜትር የጠጠር እና 459 ኪ/ሜትር ጥሪጊያ መንገድ የተለያዩ የወረዳ ቀበሌዎችን እና አጎራባች ወረዳዎችን እርስ በርስ የሚያገናኝ መንገዶች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡   

2.2 ስልክ፣ ኢንተርኔት እና የፖስታ አገልግሎት

የመደበኛ ስልክ አገልግሎት በቦምቤ እና በሞሌ ከተሞች ያለ ሲሆን የሞባይል አገልግሎት ሁሉም ቀበሌዎች ያገኛሉ፡፡ አንድ የፖስታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በቦምቤ ከተማ ይገኛል፡፡

2.3 መብራት

በወረዳው ውስጥ የሚገኙ የቦምቤ እና ፋራዎቻ ከተማ አከባቢዎች 24 ሰዓት የሃይደሮ ኤሌክትሪክ ኃይል መብራት አገልግሎት ያገኛሉ፡፡

2.4 የመጠጥ ውኃ አቅርቦት

የመጠጥ ውኃ አቅርቦትን በተመለከተ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ የእጅ ጉድጓድ (                                    ) 6፣ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ ጥልቅ ጉድጓድ (                                   ) 49፣ ጥልቅ ጉድጓድ ስርጭት (                       ) 1፣ የምንጭ ውኃ ስርጭት (                         ) 3፣ ምንጭ በቦታው ማጎልበት (           ) 18 ይገኛሉ፡፡ የወረዳው የመጠጥ ውኃ ሽፋን 56.74% ነው፡፡

2.5 የገንዘብ ተቋማት፡-

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም እንዲሁም ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት እየተከፈቱ ይገኛሉ፡፡

   . የማህበራዊ አገልግሎት

3.1 ጤና

  • ሆስፒታል /        / ------------------------ 1
  • ጤና ጣቢያ /             / ------------- 3
  • ጤና ኬላ /           / ------------------ 20
  • የመጀመሪያ ደረጃ ክሊንክ /      / --------- 8 (የግል)  
  • መድኃኒት ቤት /        / --------------- 6 (4 የመንግስት እና 2 የግል)
  • ላቦራቶሪ ---------------------------------------- 4 (የመንግስት)
  • የጤና ሽፋን ----------------------------------- 90%

3.2 ትምህርት

መዋዕለ ሕጻናት ት/ቤት -------------------------- 4

አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-4ኛ ክፍል) ------------- 9

አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-8ኛ ክፍል) -------------- 25

ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (9-10ኛ ክፍል) ------------ 2

መሰናዶ (11-12ኛ ክፍል) --------------------------- 1

 . በመስኖ የሚለማ የእርሻ መሬት ሁኔታ

በወረዳው ውስጥ 2 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ በመሆናቸው የአከባቢው አርሶ አደር ተጠቃሚ ሲሆን ለአብነት ማጌራ መስኖ በፋራዎቻ ቀበሌ (150 ሄ/ር) እና ወይቦ መስኖ በአጆራ ቀበሌ (190 ሄ/ር) የመስኖ ፕሮጀክቶች ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ወደ ሥራ የተገባ ቢሆንም 100% ተግባራዊ ባለመሆኑ የታለመውን ግብ ሊመታ አልቻለም፡፡ ይሁን እንጂ ወረዳው ካለው የከርሰምድርና የገጸምድር ውኃ አቅርቦት ለአብነት ወንዞች (ወይቦ፣ ማጌራ፣ ባሊሺያ እና ኦሞ ወንዝ) ከመኖራቸው አንጻር እስካሁን በመስኖ የለማው መሬት መጠን በጣም ዝቅተኛ ከመሆኑም ባሻገር ወረዳው ከፍተኛ ለመስኖ አገልግሎት ሊውል የሚችል የውኃ ፖቴንሻል እንዳለ፣ ከፍተኛ የዝናብ መጠን መኖሩ እና ለም ዐፈር መኖሩ ለእርሻ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡

 . በወረዳው የሚመረቱ ዋና ዋና ምርቶች

5.1 ዓመታዊ ሰብሎች

የአገዳ ሰብሎች (በቆሎ፣)፣ የጥራጥሬ ሰብሎች (ቦሎቄ፣ ባቄላ፣ አተር፣ አኩሪ አተር)፣ የብርዕ ሰብሎች (ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ)፣ የሥራ ሥር ሰብሎች (ስኳር ድንች፣ ካሳቫ፣ ጎዳሬ)፣ አትክልት (ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማትም)፣ ነጭ ሽንኩርት፣ ቅመማ ቅመም (ዝንጅብል፣ ዕርድ፣ በርበሬ/ቃሪያ)፣

5.2 ቋሚ ሰብሎች

ፍራፍሬ (ሙዝ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ አፕል)፣ ሽፈራው/ሞሪንጋ፣ እንሰት፣ ቡና፣ ጫት

 

 

  . ለኢንቨስትመንት የተዘጋጀ መሬት በሄ/ር

 ተ.

የቀበሌው ስም

(ልዩ መንደር)

ለኢንዱስትሪ  

 

ለንግድ እና  ለማህበራዊ አገልግሎት  

ለከተማ ግብርና

ለገጠር እርሻ ልማት ሊውል የሚችል መሬ

1

ቦምቤ ከተማ  

89.977ሄ/

11.7 ሄ/

42.4378

------

2

ባዳዬ ቀበሌ (ሶልኮ)

------

-----

-----

 50ሄ/ር (ለዝንጅብል፣ ዕርድ)

3

ባዳዬ ቀበሌ (ቂርቆ)

------

-----

-----

 242 ሄ/ር (ለዝንጅል)

4

አዲላ ቀበ

2 ሄ/ር

-----

-----

ለቡና/ዝንጅብል ማቀነባበ

     ምንጭ፡- ቦምቤ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት

ማሳሰቢያ፡- ለገጠር እርሻ ኢንቨስትመንት የተለዩ ቦታዎችን በተመለከተ በኢንቨስትመንት መሬት ባንክ ውስጥ ተመዝግቦና ተካልሎ በባዳዬ ቀበሌ የሚገኘው 292 ሄ/ር በተጨማሪ ከወረዳዉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት በተፋሰስ ሊለሙ የሚችሉ የወል መሬት ሰርቨይ ተደርጎ የተካለለ ሲሆን ከቦምቤ ማዘጋጃ ቤት በተገኘው መረጃ መሠረት 144.11 ሄ/ር ለተለያዩ አገልግሎቶች በከተማው መሠረታዊ ፕላን መሠረት የተዘጋጀ መሆኑን ታሳቢ ሊደረግ ይገባል፡፡

   . ለኢንቨስትመንት ያለው አመቺነት

7.1 ለግብርና

  • ሰፊ በመስኖ የሚለማ የአርሶ አደር ማሳ እና የተዘጋጀ የወል መሬት መኖሩ፣
  • ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠን ከፍተኛ መሆኑ፣
  • በወረዳው ዓመቱን ሙሉ የማይደርቁ ወንዞች ማለትም የኦሞ፣ ወይቦ፣ ማገራ እና የባሊሽያ ወንዝ እንዲሁም በተፋሰስ የለሙና የተካለሉ ሰፊ ቦታዎች ያሉት በመሆኑ በንብ ማነብ፣ በበሬ ድለባ፣ በበግ ማሞከት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣ በዘመናዊ እንሰሳት ዕርባታ፣ ለዶሮ ዕርባታ እንዲሁም ዓሳ ዕርባታ ከኦሞ ወንዝ የሰው ሠራሽ ሐይቅ እና በሰው ሠራሽ ኩሬ ለማካሄድ ምቹ መሆኑ፣
  • በልማት ሥራ ላይ ለማዋል በቂ የሰው ኃይል /የተማረ እና የጉልበት/ መኖሩ፣
  • በለሙ ተፋሰሶች እና በአርሶ አደር ማሳ የተሻሻለ መኖ፣ ምጥን መኖ፣ የተለያዩ የሰብል ተረፈ ምርቶች፣ የተፈጥሮ ግጦሽ መኖ አቅርቦት መኖሩ፤
  • እንስሳት ዕርባታ እና ድለባ ለማካሄድ ከፍተኛ የቀንድ ከብት ክምችት፣ ውኃ እና የግብይት ማዕከላት መኖሩ፤ በዞን አቀፍም ሆነ ሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የገበያ ፍላጎት መኖሩ፤
  • ለፍየሎች የቅንጠባ መኖዎች ያለባቸው ሰፋፊ የተፈጥሮ ደኖች መኖራቸው፤
  • የተሻሻለ የእንስሳት ዝሪያ እየተስፋፋ መሆኑ (በሰው ሠራሽ ዘዴ በማዳቀል)፤
  • ከፍተኛ የሀገረሰብና የተሻሻለ የበግ፣ የፍየል እና የዶሮ አቅርቦት መኖሩ፤
  • ለንብ አበባ ቀሰማ ምቹ የሆኑ የተፈጥሮ ደኖች፣ በለሙ ተፋሰሶች፣ የፍራፍሬ ዛፎች መኖራቸው፤

7.2 ለአግሮ ኢንዱስትሪ

  • ከአርሶ አደሩ የሚገኙትን የግብርና ምርቶችን (በአውትግራውር ከአርሶ አደሩ ጋር ትስስር በመፍጠር) በጥሬ ዕቃነት ተጠቅሞ በማቀነባበር እስከ ውጪ ገበያ ድረስ ለሚያቀርቡ ባለሀብቶች መሬቱ አመቺነት ያለው በመሆኑ ግብዓትን ያለውጣውርድ ማግኘት ይቻላል፤
  • ለተለያዩ ፋብሪካዎች በጥሬ ዕቃነት ሊያገለግሉ የሚችሉ የግብርና ምርቶች የሆኑ እንደ ቅመማ ቅመም (ዝንጅብል፣ ዕርድ፣ በርበሬ/ቃሪያ)፣ ቦቆሎ፣ ቦሎቄ፣ ቡና፣ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ቲማቲም፣ ሙዝ፣ ካሳቫ እና እንስሳት ሀብት በቅርበትና በበቂ ሁኔታ መገኘታቸዉ፤
  • ለእንስሳት መኖ ዝግጅት ምቹ ሁኔታ (የተፈጥሮ ሣር፣ አልፋአልፋ፣ ሉሲኒያ፣ ላብላብ፣ አኩሪ አተር፣ የርግብ አተር፣ ኤሌፈንት ሳር፣ ዴሾ ሣር፣ ወዘተ በአሁኑ ወቅት በተፋሰስ በለሙ ቦታዎች (በነዋሴ ቀበሌ፣ በኦሴ እና ባዳዬ ቀበሌ እስከ 800 ሄ/ር) እና በአርሶ አደር ማሳ በስፋት እየተመረተ በመሆኑ፣ እንዲሁም በቀላሉ ሊለማ የሚችልና በተፋሰስ ለማልማት ከ5,470 ሄ/ር መሬት በ19 የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ የተዘጋጀ በመሆኑ፤  

7.3 ለማህበራዊ አገልግሎት

የወረዳው የጤና ሽፋን 90% የደረሰ ቢሆንም በላቦራቶሪ እና በግል ፋርማሲ ተቋማት ሽፋን ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤

ከመዋዕለ ሕጻናት እስከ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ብዛት ዝቅተኛ መሆኑ እንዲሁም በከፍተኛ የት/ት ተቋማት ወይም ኮሌጆች በወረዳው ውስጥ ያለመኖር ለግል ባለሀብት በመስኩ መሰማራት አመችነቱን ይጠቁማል፡፡

7.4 ለሆቴል፣ ለሪዞርት፣ ለሎጅ፣ ለመዝነኛ ፓርክ እና ቱሪዝም አገልግሎት

  • የግልገል ጊቤ 3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ከኃይል ማመንጫነቱ ባለፈ ለቱሪስት መስህብነት፣ ለዓሳ ሀብት ልማት፣ ለትራንስፖርቴሸን አገልግሎት እንዲሁም ዘመናዊ የጀልባ አገልግሎት በመስጠት የመዝነኛ ሥራዎችን በስፋት ለማካሄድ እጅግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡
  • አሪኰሎጂ ጥናትና ምርምር እና ለቱሪስት መስህብነት ሊውሉ የሚችሉ ተፈጥሯዊ የአጆራ መንቲያ ፏፏቴዎች (በአጆራ ቀበሌ) እና የሣንጋና ፏፏቴ (ቦምቤ ገ/ማህበር ቀበሌ)፣ ታሪካዊ የሆኑ ዋሻዎች ለአብነት አሩጂያ ዋሻ (ዴንባ ሄሬጀ ቀበሌ)፣ ሰው ሠራሽ ትክል ድንጋይ (በሊባሴ እና በቦምቤ ገ/ማህበር ቀበሌ)፣ ፍል ውኃ (በኦሴ ቀበሌ)፣ ሣኣ ቱሳ (በሄሬጀ ቀበሌ) በወረዳው ውስጥ የሚገኙ በመሆናቸው የቱሪስት መስህብነት ደረጃውን ከፍ ያደርጋሉ፡፡  
  • በወረዳው ዋና ከተማም ሆነ በሌሎች የማዘጋጃ ቤቶች ውስጥ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል፣ ሎጅ፣ ሪዞርት፣ ፔንሲዮን እና የመዝነኛ ማዕከላት ያለመኖሩ በዘርፉ የገበያ ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤

7.5 ለማዕድን፣ ኢነርጂ እና ለኮንስትራክሽን ዘርፍ

ለኮንስትራክሽን የሚያገለግሉ ጥሬ ዕቃዎች በአከባቢዉ በበቂ ሁኔታ መገኘታቸዉ፣ ነጭ ድንጋይ ለግንባታ አገልግሎት የሚውል በ13 የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ፣ ጥቁር ድንጋይ ለጠጠር ማምረት የሚሆን ሲኖር በተለያዩ ቀበሌዎች ነጭ ድንጋይ (          ) የመሳሰሉት በከፍተኛ መጠን መኖሩ፤

    . የኢንቨስትመንት አማራጭ ዕድሎች

8.1 ግብርና ዘርፍ

  • አትክልትና ፍራፍሬ ልማት (ማንጎ፣ አቦካዶ፣ ሙዝ፣ ሎሚ)፣
  • ቅመማ ቅመም (ዝንጅብል፣ ዕርድ፣ በርበሬ/ቃሪያ) ልማት፣
  • የወተትና ሥጋ ከብት ማርባትና ማድለብ፣
  • በዶሮ ዕርባታና እንቁላል ምርት፣
  • በንብ ማነብ፣ በበግና ፍየል ማሞከት፣
  • የእንስሳት መኖ ዘር ማባዛትና ማልማት፣
  • የአገዳ ሰብሎችን  (በቆሎ፣) ማምረት፣
  • ቡና እና ጫት (          ) ማምረት፣  
  • የእንስሳት መኖ ዘር ማባዛትና ማልማት፣

8.2 በማህበራዊና በአገልግሎት ዘርፍ

  • በትምህርት ዘርፍ ከመዋዕለ ህፃናት እስከ ኮሌጅ፤
  • በጤና ዘርፍ በከፍተኛ ክሊኒክ፣ ላቦራቶሪ፣ ፋርማሲ፣ በእንስሳት ህክምና ማዕከላት
  • በመዝነኛ አገልግሎት ዘርፍ፡- ሲኒማ ቤቶች፣ ፊልምና ቲያትር ቤቶች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ጂም ቤቶች እና ሌሎች
  • በሆቴልና ቱሪዝም ከካፊቴሪያ፣ ግሮሰሪ፣ ፔንሲዮን እስከ ባለኮከብ ሆቴል
  • ለሎጅ፤ ለሪዞርትና መዝናኛ ማዕከል (በአጆራና ሳንጋና ፏፏቴ፣ በጊቤ ሐይቅ አከባቢ)፣
  • ነዳጅ ማደያዎች እና ከፍተኛ ጋራዥ፣
  • ሱፐር ማርኬት /የገበያ ማዕከላት፣ ሪል ስቴት ገንብቶ ማከራየት፣
  • ላውንዴሪ አገልግሎት፣
  • የጅምላ ንግድ ማከፋፈያ፣

8.3 በኢንዱስትሪ ዘርፍ

 የኢንዱስትሪ ፖቴንሻል ሰርቨይ /   / ጥናት መሠረት በከተማው ውስጥ

  • ለቅመማ ቅመም (ዝንጅብል እና ዕርድ) ማቀነባበሪያ፣
  • ለአትክልትና ፍራፍሬ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣
  • ለሥጋና የሥጋ ውጤቶች ማቀነባበሪያ፣
  • የእንስሳት መኖ ዘር ማባዣ፣ ማቀነባበሪያና ማሸጊያ ፋብሪካ፣
  • የማርና ሰም ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣
  • የብሎኬት እና የጠጠር ማምረቻ፣
  • ለሕንጻ ግንባታ የሚውል ነጭ ድንጋይ ማምረቻ፣