• Call Us
  • +251465512106

የድጉና ፋንጎ ወረዳ አስተዳደር

 አጠቃላይ ገጽታ

የዱጉና ፋንጎ ወረዳ ዋና ከተማ ቢጣና ከዞኑ ርዕሰ መዲና ሶዶ በስተምስራቅ በ46 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝና የቆዳ ስፋቱም 402 ካሬ ኪ.ሜትር ሲሆን በ27 የገጠር ቀበሌዎች እና በ6 የማዘጋጃ ቤት ከተሞች የተዋቀረ ነው፡፡ በአስተዳደሩ የሚገኙ የኢንቨስትመንት አማራጮች፤ የማዕድን ሀብት ክምችትና የቱሪስት መስህቦች እንደሚከተለዉ ቀርበዋል፡፡

1.1 ከባህር ወለል ከፍታ

ከባህር ወለል በላይ ከ1000 እስከ 2,500 ሜትር ከፍታ ያላቸው የመሬት ገጾች አሉት፡፡

1.2 የአየር ንብረት

የወረዳው አግሮኢኮሎጂን በተመለከተ 22.5% ደጋ፣ 23.4% ወይና ደጋ እና 54.1% ቆላ ነዉ፡፡ የዓመቱ አማካይ የሙቀት መጠን 17.6--22.5 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ነው፡፡ አማካይ ዓመታዊ የዝናብ መጠን ከ800 እስከ 1,200 ሚሊ ሜትር ነው፡፡

1.3 ሥነ-ሕዝብ

በ2009 ዓ.ም ከዞኑ ፋ/ኢ/ል/መምሪያ በተገኘው የስታትስቲክስ መረጃ መሠረት የወረዳው አጠቃላይ የሕዝብ ብዛት 127,971 ሲሆን የሕዝብ ጥግግት 310 በስኳየር ኪ/ሜትር ነው፡፡

 

  . የመሠረተ ልማት አቅርቦት ሁኔታ

2.1 መንገድ

የወረዳውን 3 ከተሞችን (ቀርጨጨ፣ ቢጠና እና ዲምቱ) ከሶዶ-ሐዋሳ አቋርጦ የሚያልፍ አስፋልት መንገድ እየተዘረጋ ያለ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ 36.5 ኪ/ሜትር የጠጠር እና 398.57 ኪ/ሜትር ጥሪጊያ መንገድ የተለያዩ የወረዳ ቀበሌዎችን እና አጎራባች ወረዳዎችን እርስ በርስ የሚያገናኝ መንገዶች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡   

2.2 ስልክ፣ ኢንተርኔት እና የፖስታ አገልግሎት

በወረዳው ዋና ከተማ የሞባይልና የመደበኛ ስልክ አገልግሎት፣ እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎት የሚሰጡ የግል ንግድ ማዕከላት እየተከፈቱ ይገኛሉ፡፡ አንድ የፖስታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በቢጠና ከተማ ይገኛል፡፡

2.3 መብራት

በወረዳው ውስጥ የሚገኙ የከተማ አከባቢዎች 24 ሰዓት የሃይደሮ ኤሌክትሪክ ኃይል መብራት አገልግሎት ያገኛሉ፡፡

2.4 የመጠጥ ውኃ አቅርቦት

የመጠጥ ውኃ አቅርቦትን በተመለከተ በእጅ ፓምፕ የሚሠራ የእጅ ጉድጓድ (                                    ) 3፣ ጥልቅ ጉድጓድ ስርጭት (                       ) 7፣ የምንጭ ውኃ ስርጭት (                         ) 1፣ ምንጭ ማጎልበት (           ) 5 ይገኛሉ፡፡ የወረዳው የመጠጥ ውኃ ሽፋን 36.407% ሲሆን በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ችግር ለማቃለል የጥልቅ ጓድጓድ ውኃ አገልግሎት ለመስጠት በተለያዩ ቀበሌዎች መስመር እየተዘረጋ ይገኛል፡፡

2.5 የገንዘብ ተቋማት፡-

የኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ብቻ ለወረዳው ነዋሪዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት ለመክፈት በዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡

   . የማህበራዊ አገልግሎት  

3.1 ጤና

  • ሆስፒታል /        / ------------------------ 1
  • ጤና ጣቢያ /             / ------------- 5
  • ጤና ኬላ /           / ------------------ 26
  • የመጀመሪያ ደረጃ ክሊንክ /      / --------- 10 (የግል)  
  • መድኃኒት ቤት /        / --------------- 8 (6 የመንግስት እና 2 የግል)
  • ላቦራቶሪ ---------------------------------------- 6 (የመንግስት)
  • የጤና ሽፋን ------------------------------------ 122.63%

3.2 ትምህርት

መዋዕለ ሕጻናት ት/ቤት -------------------------- 4

አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-4ኛ ክፍል) ------ -------- 8

አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-8ኛ ክፍል) -------------- 39

ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (9-10ኛ ክፍል) ------------ 7

መሰናዶ (11-12ኛ ክፍል) --------------------------- 2

  . በመስኖ የሚለማ የእርሻ መሬት ሁኔታ

በወረዳው ውስጥ 3 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ በመሆናቸው የአከባቢው አርሶ አደር ተጠቃሚ ሲሆን ለአብነት ቢላቴ ኤታ መስኖ (627.77 ሄ/ር)፣ ብላቴ ጨርቾ መስኖ (859.17 ሄ/ር) እና ፋንጎ ቢጆ መስኖ (120 ሄ/ር) የመስኖ ፕሮጀክቶች ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ አልፎ ለሀገርቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ ወረዳው ካለው የከርሰምድርና የገጸምድር ውኃ አቅርቦት ለአብነት ወንዞች (ብላቴ ወንዝ እና ጫራቄ ወንዝ) ከመኖሩ አንጻር እስካሁን በመስኖ የለማው መሬት መጠን በጣም ዝቅተኛ ከመሆኑም ባሻገር ወረዳው ከፍተኛ ለመስኖ አገልግሎት ሊውል የሚችል የውኃ ፖቴንሻል እንዳለ፣ ከፍተኛ የዝናብ መጠን መኖሩ እና ለም ዐፈር መኖሩ ለእርሻ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡

 . በወረዳው የሚመረቱ ዋና ዋና ምርቶች

5.1 ዓመታዊ ሰብሎች

በቆሎ፣ ጤፍ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ሽንብራ፣ ገብስ፣ የሥራ ሥር ሰብሎች፣ ጥጥ፣ አትክልት (ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማትም)፣ ቅመማ ቅመም (በርበሬ፣ ነጭ ሽንኩርት) ምርት፣

5.2 ቋሚ ሰብሎች

ፍራፍሬ (ሙዝ፣ ማንጎ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያ)፣ ሽፈራው፣ ካሳቫ፣ እንሰት፣ ቡና፣ ጫት፣ ሾንኮራ አገዳ፣

 

 

 

  . ለኢንቨስትመንት የተዘጋጀ መሬት

 ተ.

ለማንፋክቸሪንግ ኢንዱስት

ለንግድ እና ለማህበራዊ አገልግሎት  

ለከተማ ግብርና

ለገጠር እርሻ ልማት

1

55.6 ሄ/

6 ሄ/

26 ሄ/

300 ሄ/

  ምንጭ፡- ቢጣና ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት

ማሳሰቢያ፡- ለገጠር እርሻ ኢንቨስትመንት የተለዩ ቦታዎችን በተመለከተ በብላቴ ቀበሌ 300 ሄ/ር መሬት ከአቶ ዮናስ ሰርጎብርሃን ከተባለው ባለሀብት የተቀማ እንዲሁም በወረዳዉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት አማካይነት በተፋሰስ ሊለሙ የሚችሉ በ26 ቀበሌዎች የወል መሬት ሰርቨይ ተደርጎ የተካለለ ሲሆን ከቢጣና ማዘጋጃ ቤት በተገኘው መረጃ መሠረት 87.6 ሄ/ር ለተለያዩ አገልግሎቶች በከተማው መሠረታዊ ፕላን መሠረት የተዘጋጀ መሆኑን ታሳቢ ሊደረግ ይገባል፡፡

   . ለኢንቨስትመንት ያለው አመቺነት

7.1 ለግብርና

  • ሰፊ በመስኖ የሚለማ የአርሶ አደር ማሳ እና የወል መሬት መኖሩ፣
  • ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠን ከፍተኛ መሆኑ፣
  • በወረዳው ዓመቱን ሙሉ የማይደርቁ ወንዞች ማለትም ብላቴ ወንዝ እና ጫራቄ ወንዝ እንዲሁም በተፋሰስ የለሙና የተካለሉ ሰፊ ቦታዎች ያሉት በመሆኑ በንብ ማነብ፣ በበሬ ድለባ፣ በበግና ፍየል ማሞከት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣ በዘመናዊ እንስሳት ዕርባታ፣ ለዶሮ ዕርባታ እንዲሁም ዓሳ ዕርባታ በሰው ሰራሽ ኩሬ ለማካሄድ ምቹ መሆኗ፣
  • በልማት ሥራ ላይ ለማዋል በቂ የሰው ኃይል /የተማረ እና የጉልበት/ መኖሩ፣
  • በለሙ ተፋሰሶች እና በአርሶ አደር ማሳ የተሻሻለ መኖ፣ ምጥን መኖ፣ የተለያዩ የሰብል ተረፈ ምርቶች፣ የተፈጥሮ ግጦሽ መኖ አቅርቦት መኖሩ፤
  • እንስሳት ዕርባታ እና የዳልጋ ከብት ድለባ ለማካሄድ ከፍተኛ የቀንድ ከብት ክምችት፣ ውኃ እና የግብይት ማዕከላት መኖሩ፤ በዞን አቀፍም ሆነ ሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የገበያ ፍላጎት መኖሩ (ለአብነት ከዴንዶ ኦፋ ቀበሌ አንድ አርሶ አደር 2 በሬዎችን በማድለብ በ70,000 ብር መሸጥ መቻሉ)፤
  • ለከብቶች ጤና ተስማሚ የሆነው አሞሌ ጨው በበቂ ሁኔታ በአከባቢው መኖሩ፣
  • ለፍየሎች የቅንጠባ መኖዎች ያለባቸው ሰፋፊ የተፈጥሮ ደኖች መኖራቸው፤
  • የተሻሻለ የእንስሳት ዝሪያ እየተስፋፋ መሆኑ (በሰው ሰራሽ ዘዴ በማዳቀል)፤
  • ከፍተኛ የሀገረሰብና የተሻሻለ የበግ፣ የፍየል እና የዶሮ አቅርቦት መኖሩ፤
  • ለንብ አበባ ቀሰማ ምቹ የሆኑ የተፈጥሮ ደኖች፣ በለሙ ተፋሰሶች፣ የፍራፍሬ ዛፎች መኖራቸው፤
  • ከፍተኛ የወተት ምርት፣ የወተት እና ተዋጽኦ ምርት ፍላጎት እንዲሁም የመስሪያ ቦታና የመሠረተ ልማት አቅርቦት መኖሩ ለኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ የተመቻቹ ሁኔታዎች ናቸው፡፡

7.2 ለአግሮ ኢንዱስትሪ

  • ከአርሶ አደሩ የሚገኙትን የግብርና ምርቶችን (በአውትግራውር ከአርሶ አደሩ ጋር ትስስር በመፍጠር) በጥሬ ዕቃነት ተጠቅሞ በማቀነባበር እስከ ውጪ ገበያ ድረስ ለሚያቀርቡ ባለሀብቶች መሬቱ አመቺነት ያለው በመሆኑ ያለውጣውርድ ማግኘት ይቻላል፤
  • ለተለያዩ ፋብሪካዎች በጥሬ ዕቃነት ሊያገለግሉ የሚችሉ የግብርና ምርቶች የሆኑ እንደ ቦቆሎ፣ ቡና፣ ሾንኮራ አገዳ፣ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ቲማቲም፣ ሙዝ፣ ቦሎቄ እና እንስሳት ሀብት በቅርብ መገኘታቸዉ፤
  • የወተት እና የወተት ተዋጽኦ ለማቀነባበር ከፍተኛ የወተት ምርት መኖሩ፣
  • የሥጋ ምርት (የዳልጋ ከብት፣ የዶሮ፣ የፍየል፣ የዓሳ) ለማቀነባበር የተሻሻሉ ዝሪያ፣ የተዳቀሉ እና የሀገረሰብ ዘር አቅርቦት መኖሩ፣
  • የቆዳና ሌጦ ምርቶችን ፋብሪካ ለማቋቋም ከብላቴ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋም እና ከአጎራባች ወረዳዎች እና ዞኖች በቂ ምርት ማግኘት መቻሉ፤
  • ምጥን የከብቶች መኖ ለማዘጋጀት በቂ የግብዓት አቅርቦት እና ከፍተኛ የምርት ፍላጎት መኖሩ፤    
  • ለእንስሳት መኖ ዝግጅት ምቹ ሁኔታ (አልፋአልፋ፣ ሉሲኒያ፣ ላብላብ፣ አኩሪ አተር፣ የርግብ አተር፣ ኤሌፈንት ሳር፣ ዴሾ ሣር፣ ወዘተ በአሁኑ ወቅት በተፋሰስ በለሙ ቦታዎች በስፋት እየተመረተ በመሆኑ እንዲሁም በቀላሉ ሊለማ የሚችልና በቂ የተዘጋጀ ቦታ መኖሩ፤

7.3 ለማህበራዊ አገልግሎት

የወረዳው የጤና ሽፋን 122.63% ቢሆንም በላቦራቶሪ እና በግል ፋርማሲ ተቋማት ሽፋን ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤

የመዋዕለ ሕጻናት እና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ብዛት ዝቅተኛ መሆኑ እንዲሁም በከፍተኛ የት/ት ተቋማት ወይም ኮሌጆች በወረዳው ውስጥ ያለመኖር ለግል ባለሀብት በመስኩ መሰማራት አመችነቱን ይጠቁማል፡፡

7.4 ለሆቴል፣ ለሪዞርት፣ ለሎጅ፣ ለመዝነኛ ፓርክ እና ቱሪዝም አገልግሎት

  • የዲምቱ ፍል ውኃ (በዲምቱ ከተማ)፣ ቦሩዋ ፍል ውኃ (በፋንጎ ሁምቦ)፣ ጨርቾ ፍል ውኃ እና ዶሮንሳ ፍል ውኃ (ፋንጎ ኮይሻ) ከተለያዩ በሽታዎች በፈዋሽነት የሚታወቀውን የእንፋሎት ጭስ ፍል ውኃና በቀትርም ጭምር የሚንቦለቦለውን ለመጎበኘትና ለመዝናናት ወደ መስህቡ የሚያደርስ የአስፋልት መንገድ መኖሩ፣
  • 1805 ዓ.ም የተቋቋመ ጥንታዊ የደብሬ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በውስጡ ሐይማኖታዊና ታሪካዊ የሆኑ ከፍየል ቆዳ የተሠሩ የብራሃና መጻሐፍቶች፣ የብር ማቆሚያ፣ የንጉስ አጼ ምኒልክ ካባ (ባለብር ዘርፍ)፣ የንጉስ ካዎ ጦና ቀሚስ (ባለብር ዘርፍ)፣ ከንጉስ ኃ/ስላሴ እና ከልጃቸው ልዕልት ሮማን የተበረከተ ጻህል፣ ከ132 ዓመታት በላይ ባስቆጠሩ መካነ መቃብር ላይ የተተከሉ የወይራ እና የአልደር (ሹዋ) ወይም በተለምዶ የእግዜር ድልድይ ተብሎ የሚጠራና በአሁኑ ወቅት ከአገራችን እየጠፉ ካሉ የሀገር በቀል ዛፎች አንዱ የሆነው፣ ወዘተ አካትቶ የያዘ ታሪካዊና ጥንታዊ የሐይማኖት ተቋም በወረዳው ውስጥ በዱጉና ሶሬ ቀበሌ መኖሩ፣
  • ሰው ሠራሽ የሆኑ የዋሻ ውስጥ ጎተራዎች (የእህል ማከማቻ) ለአብነት ባታ ቁሊያ (ዴንዶ ወርቅቻ)፣ አዳ ቁሊያ (ፋንጎ ሁምቦ) እና ላማጎ ቁሊያ (በዴንዶ ኦፋ ቀበሌ)፣ የምድር ቤት ውስጥ መኖሪያ ቤት (በዴንዶ ኦፋ ቀበሌ)፤
  • የተፈጥሮ ደን ልማት (በፋንጎ ኪንዶ ቀበሌ)፣ የአቡ ተራራና የተፈጥሮ ደን (በዱጉና ቦሎሶ ቀበሌ) በወረዳው ውስጥ የሚገኙ በመሆናቸው የቱሪስት መስህብነት ደረጃውን የላቀ ያደርጋሉ፡፡
  • በወረዳው ዋና ከተማም ሆነ በሌሎች የማዘጋጃ ቤቶች ውስጥ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል፣ ሎጅ፣ ሪዞርት፣ ፔንሲዮን እና የመዝነኛ ማዕከላት ያለመኖሩ በዘርፉ የገበያ ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤     

7.5 ለማዕድን፣ ኢነርጅ እና ለኮንስትራክሽን ዘርፍ

  • ለኮንስትራክሽን የሚያገለግሉ ጥሬ እቃዎች በአከባቢዉ በበቂ ሁኔታ መገኘታቸዉ፣ ነጭ ድንጋይ፣ ጥቁር ድንጋይ፣ ጠጠር፣ አሸዋ (ከብላቴ ተፋሰስ እና ከጫራቄ ወንዝ)፣  
  • ለብሎኬት ማምረቻ አገልግሎት የሚዉል ፑሚስ ወይም ኮምቼ፣
  • ቀይ ቀላል ጋራጋንት (      ) በዴንዶ ኮይሻ ሁምቦ፣
  • የአምቦ ድንጋይ (     )፣
  • ቀይ ድንጋይ ለሕንጻ ማስዋቢያና ግንባታ እንዲሁም ለጠመነ /     / ማምረት ሊውል የሚችል ድንጋይ፣
  • ለግንባታ አገልግሎትና ለኮብል ስቶን ሥራ ሊዉል የሚችል ባዛልትክ ድንጋይ፣
  • አማራጭ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ (ከባዮ ጋዝ ሶላር ኢነረጂ) ለማምረት ከፍተኛ የእንስሳት ሀብት መኖሩ፤

    . የኢንቨስትመንት አማራጭ ዕድሎች

8.1 ግብርና ዘርፍ

  • የወተትና ሥጋ ከብት ማርባትና የዳልጋ ከብት ማድለብ፣
  • በዶሮ ዕርባታና እንቁላል ምርት፣
  • የእንስሳት መኖ ዘር ማባዛትና ማልማት፣
  • አትክልትና ፍራፍሬ ልማት (ማንጎ፣ አቦካዶ፣ ሙዝ፣ ፓፓያ)፣
  • ቅመማ ቅመም (ነጭ ሽንኩርት፣ በርበሬ/ቃሪያ) ልማት፣
  • በንብ ማነብ፣ በበግና ፍየል ማሞከት፣
  • የአገዳ ሰብሎችን ማምረት፣
  • ቡና፣ ጫት እና ለሌሎች ገበያ ተኮር ሰብሎችን ማምረት፣

8.2 በማህበራዊና በአገልግሎት ዘርፍ

  • በሆቴልና ቱሪዝም ከካፌ እስከ ባለኮከብ ሆቴል
  • ነዳጅ ማደያዎች እና ከፍተኛ ጋራዥ፣
  • ሱፐር ማርኬት /የገበያ ማዕከላት፣ ሪል ስቴት ገንብቶ ማከራየት፣
  • ላውንዴሪ አገልግሎት፣
  • የጅምላ ንግድ ማከፋፈያ፣
  • በትምህርት ዘርፍ ከመዋዕለ ህፃናት እስከ ኮሌጅ፤
  • በጤና ዘርፍ በክሊኒክ፣ ላቦራቶሪ፣ ፋርማሲ፣ በእንስሳት ህክምና ማዕከላት፣
  • በመዝነኛ አገልግሎት ዘርፍ፡- ሲኒማ ቤቶች፣ ፊልምና ቲያትር ቤቶች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ጂም ቤቶች እና ሌሎች
  • ለሎጅ፤ ለሪዞርትና መዝናኛ ማዕከል

8.3 በኢንዱስትሪ ዘርፍ

የኢንዱስትሪ ፖቴንሻል ሰርቨይ /   / ጥናት መሠረት በከተማው ውስጥ

  • ለምግብና ምግብ ውጤቶች ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣
  • ለሥጋና የሥጋ ውጤቶች ማቀነባበሪያ፣
  • የወተትና የወተት ውጤቶች ማቀነባበሪያ፣
  • ለአትክልትና ፍራፍሬ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣
  • የቆዳና ሌጦ ምርቶችን ማምረቻ ፋብሪካ፣
  • የእንስሳት መኖ ዘር ማባዣ፣ ማቀነባበሪያና ማሸጊያ ፋብሪካ፣
  • የማርና ሰም ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣
  • የብሎኬት እና የጠጠር ማምረቻ፣