• Call Us
  • +251465512106

የዳሞት ወይዴ ወረዳ አስተዳደር

 አጠቃላይ ገጽታ                      

የዳሞት ወይዴ ወረዳ ዋና ከተማ በዴሳ ከዞኑ ርዕሰ መዲና ሶዶ በስተምስራቅ በ25 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝና የቆዳ ስፋቱም 352 ካሬ ኪ/ሜትር ሲሆን በ23 የገጠር ቀበሌዎች እና በ4 የማዘጋጃ ቤት ከተሞች የተዋቀረ ነው፡፡ በአስተዳደሩ የሚገኙ የኢንቨስትመንት አማራጮች፤ የማዕድን ሀብት ክምችትና የቱሪስት መስህቦች እንደሚከተለዉ ቀርበዋል፡፡

1.1 ከባህር ወለል ከፍታ

ከባህር ወለል በላይ ከ1,001 እስከ 2,500 ሜትር ከፍታ ያላቸው የመሬት ገጾች አሉት፡፡

1.2 የአየር ንብረት

የወረዳው አግሮኢኮሎጂን በተመለከተ 5% ደጋ፣ 60% ወይና ደጋ እና 35% ቆላ ነዉ፡፡ የዓመቱ አማካይ የሙቀት መጠን 17.6--25 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ነው፡፡ አማካይ ዓመታዊ የዝናብ መጠን ከ1,001 እስከ 1,400 ሚሊ ሜትር ነው፡፡

1.3 ሥነ-ሕዝብ

በ2009 ዓ.ም ከዞኑ ፋ/ኢ/ል/መምሪያ በተገኘው የስታትስቲክስ መረጃ መሠረት የወረዳው አጠቃላይ የሕዝብ ብዛት 124,784 ሲሆን የሕዝብ ጥግግት 337 በስኳየር ኪ/ሜትር ነው፡፡

  . የመሠረተ ልማት አቅርቦት ሁኔታ  

2.1 መንገድ

የወረዳውን ዋና ከተማ በዴሳ ከሶዶ-ሐዋሳ አቋርጦ የሚያልፍ 26 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ የተዘረጋ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ 41 ኪ/ሜትር የጠጠር እና 960 ኪ/ሜትር ጥሪጊያ መንገድ የተለያዩ የወረዳ ቀበሌዎችን እና አጎራባች ወረዳዎችን እርስ በርስ የሚያገናኝ መንገዶች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

2.2 ስልክ፣ ኢንተርኔት እና የፖስታ አገልግሎት

የሞባይልና የመደበኛ ስልክ አገልግሎት፣ እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎት የሚሰጡ የግል ንግድ ማዕከሎች እየተከፈቱ ይገኛሉ፡፡ አንድ የፖስታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በበዴሳ ከተማ ይገኛል፡፡

2.3 መብራት

በወረዳው ውስጥ የሚገኙ የከተማ አከባቢዎች 24 ሰዓት የሃይደሮ ኤሌክትሪክ ኃይል መብራት አገልግሎት ያገኛሉ፡፡

 

2.4 የመጠጥ ውኃ አቅርቦት

የመጠጥ ውኃ አቅርቦትን በተመለከተ የጥልቅ ጉድጓድ ስርጭት (                       ) 2፣ የምንጭ ውኃ ስርጭት (                         ) 3፣ ምንጭ ማጎልበት (           ) 10 ይገኛሉ፡፡ የወረዳው የመጠጥ ውኃ ሽፋን 57.84% ሲሆን በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ችግር ለማቃለል የጥልቅ ጓድጓድ ውኃ አገልግሎት ለመስጠት በተለያዩ ቀበሌዎች መስመር እየተዘረጋ ይገኛል፡፡

2.5 የገንዘብ ተቋማት፡-

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ለወረዳው ነዋሪዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡

   . የማህበራዊ አገልግሎት    

3.1 ጤና

  • ጤና ጣቢያ /             / ------------- 4
  • ጤና ኬላ /           / ------------------ 27
  • የመጀመሪያ ደረጃ ክሊንክ /      / -------- 5 (የግል)  
  • መድኃኒት ቤት /        / --------------- 5 (4 የመንግስት እና 1 የግል)
  • ላቦራቶሪ ---------------------------------------- 4 (የመንግስት)
  • የጤና ሽፋን ------------------------------------ 85.79%

3.2 ትምህርት

መዋዕለ ሕጻናት ት/ቤት -------------------------- 3

አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-4ኛ ክፍል) -------------- 2

አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (1-8ኛ ክፍል) -------------- 31

ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (9-10ኛ ክፍል) ------------ 3

መሰናዶ (11-12ኛ ክፍል) --------------------------- 1

የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ፖሊቴክኒክ ----------- 1 (አገልግሎት መስጠት ያልጀመረ)

  . በመስኖ የሚለማ የእርሻ መሬት ሁኔታ                         

በወረዳው ውስጥ 2 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ በመሆናቸው የአከባቢው አርሶ አደር ተጠቃሚ ሲሆን ለአብነት ቢሳሬ መስኖ (180.58 ሄ/ር) እና በዴሳ መስኖ (80 ሄ/ር) የመስኖ ፕሮጀክቶች 100% አገልግሎት መስጠት ባይጀምሩም ለአከባቢው ማህበረሰብ ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ አንጻር አዎንታዊ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ ወረዳው ካለው የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውኃ አቅርቦት ለአብነት ወንዞች (ቢሳሬ ወንዝ እና በዴሳ ወንዝ) ከመኖሩ አንጻር እስካሁን በመስኖ የለማው መሬት መጠን በጣም ዝቅተኛ ከመሆኑም ባሻገር ወረዳው ከፍተኛ ለመስኖ አገልግሎት ሊውል የሚችል የውኃ ፖቴንሻል እንዳለ፣ ከፍተኛ የዝናብ መጠን መኖሩ እና ለም ዐፈር መኖሩ ለእርሻ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡

 . በወረዳው የሚመረቱ ዋና ዋና ምርቶች  

5.1 ዓመታዊ ሰብሎች

በቆሎ፣ ጤፍ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ሽንብራ፣ ገብስ፣ የሥራ ሥር ሰብሎች፣ ጥጥ፣ አትክልት (ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማትም)፣ ቅመማ ቅመም ምርት፣

5.2 ቋሚ ሰብሎች

ፍራፍሬ (ሙዝ፣ ማንጎ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን፣ ሎሚ)፣ ሽፈራው/ሞሪንጋ፣ ካሳቫ፣ እንሰት፣ ቡና፣ ጫት፣ ሾንኮራ አገዳ፣

   . ለኢንቨስትመንት የተዘጋጀ መሬት

ተ.

ለኢንዱስትሪ

በሄ/ር  

ለንግድ እና ለማህበራዊ አገልግሎት በሄ/ር

ለከተማ ግብርና በሄ/

ለገጠር እርሻ ልማት በሄ/

1

138.7

22.9

85.34

550 ሄ/

    ምንጭ፡- በዴሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት

ማሳሰቢያ፡- ለገጠር እርሻ ኢንቨስትመንት የተለዩ ቦታዎችን በተመለከተ በኤሎ ኤራሾ ቀበሌ ቀበሌ 550 ሄ/ር መሬት ከባለሀብቶች የተቀማ እና የተቀነሰ መሬት በተጨማሪ በወረዳዉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት አማካይነት በተፋሰስ ሊለሙ የሚችሉ በ23 ቀበሌዎች የወል መሬት ሰርቨይ ተደርጎ የተካለለው ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሊውል የሚችል ሲሆን ከበዴሣ ማዘጋጃ ቤት በተገኘው መረጃ መሠረት ከ246 ሄ/ር በላይ መሬት ለተለያዩ አገልግሎቶች በከተማው መሠረታዊ ፕላን መሠረት የተዘጋጀ መሆኑን ታሳቢ ሊደረግ ይገባል፡፡

   . ለኢንቨስትመንት ያለው አመቺነት

7.1 ለግብርና

  • ሰፊ በመስኖ የሚለማ የአርሶ አደር ማሳ እና የወል መሬት መኖሩ፣
  • ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠን ከፍተኛ መሆኑ፣
  • በወረዳው ውስጥ ያሉ ወንዞች ማለትም በዴሳ ወንዝ እና ቢሳሬ ወንዝ እንዲሁም በተፋሰስ የለሙና የተካለሉ ሰፊ ቦታዎች ያሉት በመሆኑ በንብ ማነብ፣ በበሬ ድለባ፣ በበግና ፍየል ማሞከት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣ በዘመናዊ እንስሳት ዕርባታ፣ ለዶሮ ዕርባታ እንዲሁም ዓሳ ዕርባታ በሰው ሰራሽ ኩሬ ለማካሄድ ምቹ መሆኗ፣
  • በልማት ሥራ ላይ ለማዋል በቂ የሰው ኃይል /የተማረ እና የጉልበት/ መኖሩ፣
  • በለሙ ተፋሰሶች እና በአርሶ አደር ማሳ የተሻሻለ መኖ፣ ምጥን መኖ፣ የተለያዩ የሰብል ተረፈ ምርቶች፣ የተፈጥሮ ግጦሽ መኖ አቅርቦት መኖሩ፤
  • እንስሳት ዕርባታ እና የዳልጋ ከብት ድለባ ለማካሄድ ከፍተኛ የቀንድ ከብት ክምችት፣ ውኃ እና የግብይት ማዕከላት መኖሩ፤ በዞን አቀፍም ሆነ ሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የገበያ ፍላጎት መኖሩ፣
  • ለፍየሎች የቅንጠባ መኖዎች ያለባቸው ሰፋፊ የተፈጥሮ ደኖች መኖራቸው፤
  • የተሻሻለ የእንስሳት ዝሪያ እየተስፋፋ መሆኑ (በሰው ሰራሽ ዘዴ በማዳቀል)፤
  • ከፍተኛ የሀገረሰብና የተሻሻለ የበግ፣ የፍየል እና የዶሮ አቅርቦት መኖሩ፤
  • ለንብ አበባ ቀሰማ ምቹ የሆኑ የተፈጥሮ ደኖች፣ በለሙ ተፋሰሶች፣ የፍራፍሬ ዛፎች መኖራቸው፤
  • ከፍተኛ የወተት ምርት፣ የወተት እና ተዋጽኦ ምርት ፍላጎት እንዲሁም የመስሪያ ቦታና የመሠረተ ልማት አቅርቦት መኖሩ ለኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ የተመቻቹ ሁኔታዎች ናቸው፡፡

7.2 ለአግሮ ኢንዱስትሪ

  • ከአርሶ አደሩ የሚገኙትን የግብርና ምርቶችን (በአውትግራውር ከአርሶ አደሩ ጋር ትስስር በመፍጠር) በጥሬ ዕቃነት ተጠቅሞ በማቀነባበር እስከ ውጪ ገበያ ድረስ ለሚያቀርቡ ባለሀብቶች መሬቱ አመቺነት ያለው በመሆኑ ያለውጣውርድ ማግኘት ይቻላል፤
  • ለተለያዩ ፋብሪካዎች በጥሬ ዕቃነት ሊያገለግሉ የሚችሉ የግብርና ምርቶች የሆኑ እንደ አቮካዶ፣ ቡና፣ ቲማቲም፣ ሙዝ፣ ቦሎቄ እና እንስሳት ሀብት በቅርብ መገኘታቸዉ፤
  • የወተት እና የወተት ተዋጽኦ ለማቀነባበር ከፍተኛ የወተት ምርት መኖሩ፣
  • የሥጋ ምርት (የዳልጋ ከብት፣ የዶሮ፣ የፍየል፣ የዓሳ) ለማቀነባበር የተሻሻሉ ዝሪያ፣ የተዳቀሉ እና የሀገረሰብ ዘር አቅርቦት መኖሩ፣
  • ምጥን የከብቶች መኖ ለማዘጋጀት በቂ የግብዓት አቅርቦት እና ከፍተኛ የምርት ፍላጎት መኖሩ፤ በአሁኑ ወቅት በተፋሰስ በለሙ ቦታዎች በስፋት እየተመረተ በመሆኑ እንዲሁም በቀላሉ ሊለማ የሚችልና በቂ የተዘጋጀ ቦታ መኖሩ፤   

7.3 ለማህበራዊ አገልግሎት

የወረዳው የጤና ሽፋን 85.79% ደረሰ ቢሆንም በላቦራቶሪ እና በግል ፋርማሲ ተቋማት ሽፋን ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤

የመዋዕለ ሕጻናት እና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ብዛት ዝቅተኛ መሆኑ እንዲሁም በከፍተኛ የት/ት ተቋማት ወይም ኮሌጆች በወረዳው ውስጥ ያለመኖር ለግል ባለሀብት በመስኩ መሰማራት አመችነቱን ይጠቁማል፡፡

7.4 ለሆቴል፣ ለሪዞርት፣ ለሎጅ፣ ለመዝነኛ ፓርክ እና ቱሪዝም አገልግሎት

  • የቢልቦ ፍል ውኃ (በበዴሳ ከተማ አከባቢ) ከተለያዩ በሽታዎች በፈዋሽነት የሚታወቀውን ለመጎበኘትና ለመዝናናት ምቹ መሆኑ፣
  • በበዴሳ ከተማ ውስጥ የሚገኘው የባንባሌ ተንጠልጣይ ድልድይ (Suspension Bridge) እና የአከባቢው ተፈጥሯዊ አቀማመጥ ለሠርግ፣ ለሽርሽር ከመዋል ባለፈ ለሎጅ እና ለሪዞርት ግንባታ ምቹ ሁኔታን የፈጠረ መሆኑ፣
  • የበዴሳ ፏፏቴ (በበዴሳ ከተማ) እና የባዳ ፏፏቴ (በኦሎላ ቀበሌ)፣ ታሪካዊ የሆኑ ዋሻዎች ለአብነት የኦሎላ ዋሻ (በኦሎላ ቀበሌ)፣ ጥንታዊ የነገስታት መናገሻ ገዳም (በበዴሳ ከተማ)፣
  • የተፈጥሮ ደን ልማት (በኪንዶ ኮዮ ቀበሌ)፣ የዝግባ ደን (በአዴ ዳዌ ሙንዳጃ ቀበሌ)፣ ዕድሜ-ጠገብ የዋርካ እና የዝግባ እንጨቶች (ከ1880 ዓ.ም ጀምሮ የቆየ) የመሳሰሉት በወረዳው ውስጥ የሚገኝ በመሆናቸው የቱሪስት መስህብነት ደረጃውን የላቀ ያደርጋሉ፡፡
  • በወረዳው ዋና ከተማም ሆነ በሌሎች የማዘጋጃ ቤቶች ውስጥ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል፣ ሎጅ፣ ሪዞርት፣ ፔንሲዮን እና የመዝነኛ ማዕከላት ያለመኖሩ በዘርፉ የገበያ ክፍተት መኖሩን ያሳያል፤     

7.5 ለማዕድን፣ ኢነርጅ እና ለኮንስትራክሽን ዘርፍ

  • ለኮንስትራክሽን የሚያገለግሉ ጥሬ ዕቃዎች በአከባቢዉ በበቂ ሁኔታ መገኘታቸዉ፣ ነጭ ድንጋይ (3 ሄ/ር በኤሎ ኤራሾ ቀበሌ)፣ ጥቁር ድንጋይ (2.6 ሄ/ር በበዴሳ ከተማ አከባቢ፣ በኤሎ ኤራሾ እና በቶራ ሳዴቦ ቀበሌዎች)፣ አሸዋ (12.4 ሄ/ር)፣ ቀይ ቀላል ጋራጋንት (      ) በቶራ ሳዴቦ ቀበሌ የመሳሰሉት በከፍተኛ መጠን መኖሩ፤
  • ለብሎኬት ማምረቻ አገልግሎት የሚዉል ፑሚስ ወይም ኮምቼ (በጭፍሣ ቀበሌ)፣
  • ለግንባታ አገልግሎትና ለጠጠር እና ለኮብል ስቶን ምርት ሊዉል የሚችል ባዛልትክ ድንጋይ (በኤሎ ኤራሾ፣ በአዴቻ፣ ሞጣላ እና በኦሎባ ቀበሌዎች)፣
  • የታሸገ የማዕድን ውኃ ለማምረት የቢልቦ በዴሳ እና የሃይድራም ውኃ ምንጮች ሊውሉ የሚችሉ መሆናቸው፤

 

 

 

    . የኢንቨስትመንት አማራጭ ዕድሎች ባለሀብቶች

8.1 ግብርና ዘርፍ

  • የወተትና ሥጋ ከብት ማርባትና የዳልጋ ከብት ማድለብ፣
  • በዶሮ ዕርባታና እንቁላል ምርት፣
  • የእንስሳት መኖ ዘር ማባዛትና ማልማት፣
  • አትክልትና ፍራፍሬ ልማት (ማንጎ፣ አቦካዶ፣ ሙዝ፣ ፓፓያ፣ ሎሚ)፣
  • ቅመማ ቅመም (ነጭ ሽንኩርት፣ በርበሬ/ቃሪያ) ልማት፣
  • በንብ ማነብ፣ በበግና ፍየል ማሞከት፣
  • የአገዳ ሰብሎችን ማምረት፣
  • ቡና፣ ጫት እና ለሌሎች ገበያ ተኮር ሰብሎችን ማምረት፣
  • የካሳቫ፣ ሽፈራው/ሞሪንጋ ማምረት፣

8.2 በማህበራዊና በአገልግሎት ዘርፍ

  • በሆቴልና ቱሪዝም ከካፌ እስከ ባለኮከብ ሆቴል
  • ነዳጅ ማደያዎች እና ከፍተኛ ጋራዥ፣
  • ሱፐር ማርኬት /የገበያ ማዕከላት፣ ሪል ስቴት ገንብቶ ማከራየት፣
  • ላውንዴሪ አገልግሎት፣
  • የጅምላ ንግድ ማከፋፈያ፣
  • በትምህርት ዘርፍ ከመዋዕለ ህፃናት እስከ ኮሌጅ፤
  • በጤና ዘርፍ በክሊኒክ፣ ላቦራቶሪ፣ ፋርማሲ፣ በእንስሳት ህክምና ማዕከላት፣
  • ለሎጅ፤ ለሪዞርትና መዝናኛ ማዕከል
  • በመዝነኛ አገልግሎት ዘርፍ፡- ሲኒማ ቤቶች፣ ፊልምና ቲያትር ቤቶች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ጂም ቤቶች እና ሌሎች፣

8.3 በኢንዱስትሪ ዘርፍ፡- የኢንዱስትሪ ፖቴንሻል ሰርቨይ /   / ጥናት መሠረት በከተማው ውስጥ

  • ለምግብና ምግብ ውጤቶች ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣
  • ለሥጋና የሥጋ ውጤቶች ማቀነባበሪያ፣
  • የወተትና የወተት ውጤቶች ማቀነባበሪያ፣
  • ለአትክልትና ፍራፍሬ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣ የካሳቫ፣ ሽፈራው/ሞሪንጋ ማቀነባበሪያ፣
  • የእንስሳት መኖ ዘር ማባዣ፣ ማቀነባበሪያና ማሸጊያ ፋብሪካ፣
  • የብሎኬት እና የጠጠር ማምረቻ፣ በቡና መፈልፈያና ማቀነባበሪያ፣
  • የማዕድን ውኃ ማሸጊያ ፋብሪካ፣ የፍራፍሬ ጁስ ማቀነባበር፣